Popular Posts

Friday, August 31, 2018

የአዲስ ዓመት ውሳኔ - ስለ ኢየሱስ አዳኝነት ለሰዎች መናገር


በምድር ላይ ያለንበት አንደኛውና ዋናው ምክኒያት በኑሮ እና በቃል ስለእግዚአብሄር ልጅ ኢየሱስ ክርሶስ አዳኝነት ለሌሎች እንድንመሰከር ነው፡፡
እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤ 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፡9
መንፈስ ቅዱስ የሰዎችን ህይወት ስለሃጢያት የሚወቅሰው የምንኖረውን ነፁህ ኑሮና የምንናገረው የምስክርነት ቃል ተጠቅሞ ነው፡፡
እርሱም መጥቶ ስለ ኃጢአት ስለ ጽድቅም ስለ ፍርድም ዓለምን ይወቅሳል፤ ስለ ኃጢአት፥ በእኔ ስለማያምኑ ነው፤ የዮሐንስ ወንጌል 16፡8-10
የእግዚአብሄር መንፈስ ንግግራችንን ተጠቅሞ ሰዎችን ስለሚወቅስ ማን ሰማ? ማን ተቀበለ? ማን ዳነ? ብለን ሳንጠይቅ ባገኘነው አጋጣሚ ስለ ኢየሱስ አዳኝነት ለሰዎች መመስከር ይገባናል፡፡
ከእግዚአብሔርም ዘንድ ረድኤት ተቀብዬ ለታናሹም ለታላቁም ስመሰክር እስከዚች ቀን ድረስ ቆሜአለሁ፤ ነቢያትና ሙሴ ይሆን ዘንድ ያለውን፥ ክርስቶስ መከራን እንዲቀበል በሙታንም ትንሣኤ ለሕዝብና ለአሕዛብ ብርሃንን በመጀመሪያ ሊሰብክ እንዳለው፥ ከተናገሩት በቀር አንድ ስንኳ የተናገርሁት የለም። የሐዋርያት ሥራ 26፡22-23
የሰይጣን አላማ በተቃዋሚዎች ተቃውሞ ተጠቅሞ እኛን ዝም ማሰኘት ነው፡፡ እኛ ግን ወንጌልን ስንናገር የሚቃወኑ እነዳሉ ሁሉ የሚሰሙና የሚድኑ እንዳሉ አውቀን ዝም ማለት የለብንም፡፡
የሙታንንም ትንሣኤ በሰሙ ጊዜ እኵሌቶቹ አፌዙበት፥ እኵሌቶቹ ግን፦ ስለዚህ ነገር ሁለተኛ እንሰማሃለን አሉት። አንዳንዶች ወንዶች ግን ተባብረው አመኑ፤ የሐዋርያት ሥራ 17፡32፣34
በተቃውሞ መፍራት የለብንም፡፡ ፈዝንና ስድብን አንፈራም አናከብርም፡፡ ወንጌልን ለመመስከር ነፍሳችን በእኛ ዘንድ እንደማትከብር እንደ ከንቱ ነገር መቁጠር ይጠብቅብናል፡፡  
ነገር ግን ሩጫዬንና ከጌታ ከኢየሱስ የተቀበልሁትን አገልግሎት እርሱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌልን መመስከር እፈጽም ዘንድ ነፍሴን በእኔ ዘንድ እንደማትከብር እንደ ከንቱ ነገር እቆጥራለሁ። የሐዋርያት ሥራ 20፡24
ሰዎች ዛሬ ይቀበሉ ነገ አናውቅም፡፡ የእኛ ሃላፊነት የመዳንን እውቀት ለሰዎች መስጠት ነው፡፡
ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡9-10
በአዲሱ አመት በቀን አንድ ሁለት ሶስት ሰው እያልን ስለጌታ የሱስ ከሃጢያት አዳኝነት ለመመስከር ራሳችንን መስጠት አለብን፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ወንጌል #ስብከት #ቃል #ዝራ #የምድርጨው #የአለምብርሃን #የአመፃገንዘብ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment