Popular Posts

Thursday, August 30, 2018

የሙስና አስከፊ ገፅታ

ሙስና ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም ወይም በማጭበርበር ለግል የተለየ ጥቅም ማግኘት ሲሆን ሰዎች ያልተገባቸውን ነገር ለማድረግ የተገባቸውን ነገር ለመከልከል ጉቦ በመቀበልም በመስጠትም ሊገለጥ ይችላል፡፡
አንድ አገር የሚያድገው ህብረተሰቡ በነፃነት ያለውን እውቅትና ገንዘብ አውጥቶ ለብዙዎች ጥቅም ሲጠቀም ሲሰራና እና ሲያድግ ነው፡፡ ሰዎች ቢሮክራሲው ሳይበዛና ሳያማርራቸው ጉልበታችውንና እውቀታቸውን አውጥተው ከሰሩ የግለሰቦች እድገት የአገርን እድገት ያመጣል፡፡
ለምሳሌ አንድ ሰው ያለውን የስራ ፈጠራ ክህሎት ተጠቅሞ ስራ ቢጀምር ስራው ቢያድግለትና ስራው ያለብዙ ቢሮክራሲ በመንግስት ቢያስመዘግብ ከመንግስት እርዳታ ቢያገኝና በነፃነት ቢሰራ ያስዳል በስሩ የሚቀጥራቸውም ሰዎች ያድጋሉ፡፡ ስራወ ባደገ ቁጥር ድግሞ ለምግስት የሚያስገባው ቀረጥ ያድጋል የሚቀጥራቸው ሰዎች ብብዛትመ በክፍያም አያደጉ ይሄዳሉ፡፡
ሰው በነፃነት ከመንግስት ባለስልጣኖች ሳይጉላላ እንዲሁም በየደረጃው ጉቦ እንዲከፍል ሳይገደድ በነፃነት በመልካም ውድድር ከሰራ ድርጅቱ ያድጋል በስሩ የሚሰሩ ተቀጣሪዎች ያድጋሉ አገሪቱም ታድጋለች፡፡
ነገር ግን ሙስና ባለበት ሁኔታ የሚያድጉት ሙሰኞች የመንግስት ባለስልጣኖችን በገንዘብ ጥቅም በማታለል የማይገባቸውን የሚያገኙ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ ብዙዎች ሳይሆን ጥቂቶች ብቻቸውን በሙስና እንደ ተፈንጣሪ ኮከብ በፍጥነት ወደላይ የሚወጡበት ብቻቸውን የሚያድጉበት እድገቱ ለብዙዎች ጥቅም የማይውልበት ሰው ሰራሽ እድገት ይሆናል፡፡
የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል፤ ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። መፅሃፈ ምሳሌ 28፡20
እነዚህ ሙሰኞች ገንዘባቸውን በስራ ላይ በማዋል ብዙዎችን ቀጥረው በማሰራት ከሌሎች ጋር አብረው ከማደግ ይልቅ ብቻቸውን ፈጥነው ለማደግ ባላቸው ክፉ ምኞት ባለስለጣኖችን በጉቦ በማታለል ብዙ ሰዎችን ይጎዳሉ፡፡ በሙስና የሚጎዳው በድርጅቱ ተቀጥረው መስራትና ማደግ የነበረባቸው ተቀጣሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ጉቦ የማይሰጡ ጉቦ ባለመሰጠታቸው የፈቃድና የግብር ስርአቱ የሚጠብቅባቸውና የሚያማርራቸው ሰዎች ናቸው፡፡ እግዚአብሄር የእነዚህን ሰዎች እንባ ያያል፡፡ ሙሰኛ ሰው ግብር በመክፈል ለብዙሃን መንገድ ድልድይና እና ተቋማት መገንባት አስተዋፅኦ ማድረግ ሲገባው ከደሃ ነጥቆ ከመንግስት ደሞዝ ለሚከፈለው ባለስልጣን ጉቦ በመስጠት ለባለጠጋ ይሰጣል፡፡
ይህ ሙሰኛ ግብር በመክፈል ለህብረተሰቡ መመለስ ያለበትን ገንዘብ ከደሃ ነጥቆ በመንግስት ደሞዝ ለሚከፈለው በአንፃራዊነት ለባለጠጋ ለሆነ ሰው በመስጠት እግዚአብሄርን ያሳዝናል፡፡ ሙሰኛ ሰው በተዘዋዋሪ ደሃን ይጎዳል፡፡ ሙሰኛ በክፉ ምኞቱ ወደ ድህነት ይወድቃል፡፡
ለራሱ ጥቅም ለመጨመር ሲል ድሀን የሚጐዳ፥ ለባለጠጋም የሚሰጥ፥ እርሱ ወደ ድህነት ይወድቃል። መጽሐፈ ምሳሌ 22፡16
እግዚአብሄር ህዝቡን ስለሚወድ ሙሰኞችን በተያየ መልኩ ያስጠነቅቃል፡፡ በግብር አሰባሰብ የተሰማሩትን ሙሰኛ ባለስልጣኖች እንዲመለሱ እግዚአብሄር እድልን ይሰጣቸዋል፡፡
ቀራጮችም ደግሞ ሊጠመቁ መጥተው፦ መምህር ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉት። ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ አላቸው። የሉቃስ ወንጌል 3፡12-13
እግዚአብሄር ወደ እርሱ የሚጮኸውን የደሃውን ጩኸት ስለሚሰማ በስልጣናቸው አላግባብ የሚጠቀሙትንና ከደሞዛቸቸው በላይ ጥቀም ለማግኘት የሚገባውን የሚከለክሉትን የማየገባውን የሚሰጡትን ማናቸውንም ባለስልጣናት ያስጠነቅቃል፡፡
ጭፍሮችም ደግሞ፦ እኛ ደግሞ ምን እናድርግ? ብለው ይጠይቁት ነበር። እርሱም፦ በማንም ግፍ አትሥሩ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፥ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ አላቸው። የሉቃስ ወንጌል 3፡14
እግዚአብሄር ደጋግሞ ተናግሮ ካልተመለሱ ግን ስብራታቸው ድንገት ይሆናል፡፡ በሙስና ከደሃ ቀምተው ለባለጠጋ የሚሰጡ ሰዎችም ይሁን ከድሃ ተቀምቶ እንዲሰጣቸው ሰዎችን የሚያጎሳቁሉ ሰዎች ስብራታቸው ድንገት ይሆናል ፈውስም አይኖራቸውም፡፡  
ብዙ ጊዜ ተዘልፎ አንገቱን ያደነደነ ድንገት ይሰበራል፥ ፈውስም የለውም። ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል፤ ኀጥኣን በሠለጠኑ ጊዜ ግን ሕዝብ ያለቅሳል። መጽሐፈ ምሳሌ 29፡1-2
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ባለስልጣን #ሙስና #ጉቦ #ፀሎት #ወታደር #ቀራጭ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ወንጌል #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment