Popular Posts

Friday, July 29, 2016

ተቃወሙ!


የዲያቢሎስ አላማ አንድና አንድ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከመጣ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ለሌላ ነገር አይመጣም፡፡   


ዲያቢሎስንብ የመጋዣው መንገድ ደግሞ በእግዚአብሄር ላይ ማመፅ ወደ እግዚአብሄር አለመጠጋትና ከሃጢያት ጋር መጫወት ነው፡፡ 


ዋነኛው ታዲያ ዲያቢሎስን የመቃወሚያው መንገድ ለእግዚአብሄር መገዛት ነው፡፡ ዲያቢሎስን የመቃወም ውጤታማው መንገድ ወደ እግዚአብሄር መቅረብ ነው፡፡ 


እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ። ያዕቆብ 4፡7-8


ልጆች ሆነን ሸንኮራ ስንመጥ የምንጥለው ምጣጭ ዝንብን ይስባል፡፡ ዝንብን መከላከያው ውጤታማው መንገድ የዝንብ ማባረሪያና መግደያ አይደለም፡፡ ምክኒያቱም ዝንብን የሚስበው ቆሻሻ ስለሆነ ቆሻሻው እስካለ ድረስ ሁሌ ዝንብ ይሳባል፡፡ ዝንብ ቆሻሻን ማሳደድ ተፈጥሮው ስለሆነ ቆሻሻን አስቀምጠን ዝንብ አይምጣ ማለት አንችልም፡፡ 


ነገር ግን ዝንብን የማባረሪያው መንገድ አካባቢን ማፅዳት ነው፡፡ አካባቢውን ከፀዳ ዝንብ ቢመጣ እንኳን የሚፈልገውን ስለማያገኝና እዚያ አካባቢ መቆየት ስራ መፍታትና ጊዜ ማባከን ስለሚሆንበት ዝንብ አይቆይም፡፡ 


እንዲሁ ሰይጣንን በህይወታችን እንዳይሰርቅ እንዳያርድና እንዳያጠፋ የምናደርግበት ዋነኛው መንገድ ሀጥያትን መፀየፍ ከክፉ የወጣትነት ምኞት መሸሽ ነው፡፡ 


ሰው ፍምን በብብቱ ታቅፎ አያቃጥለኝ ማለት እንደማይችል ሁሉ ሃጢያትን እየሰራ ሰይጣን አይስረቀኝ ማለት አይችልም፡፡ ሰው ለሰይጣን ተስማሚ ለም መሬት የሆነውን ጥላቻን በልቡ ይዞ ሰይጣን በህይወቴ አያጥፋ አይግደል የማለት አቅሙ አይኖረውም፡፡ 


ለሰይጣን ፍቱምን መድሃኒቱ እርሱን የሚስቡትን ነገሮች ሃጢያትንና ጥላቻን ከህይወት ማራቅ ነው፡፡ ሰይጣንን የመቃወሚያው መንገድ ለእግዚአብሄር እንደቃሉ መገዛትና ወደ እግዚአብሄር መቅረብ ነው፡፡ 


ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ 


ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes


#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment