Popular Posts

Saturday, July 16, 2016

የአይን መከፈት

ጌታ እየሱስን ተቀብለን የዚህ የእግዚአብሄር መንግስትን ጥቅሞች ተጠቃሚ እንዳንሆን የሚያደርገው አንዱ ምክኒያት መንፈሳዊ እውርነት ወይም የአይን አለመከፈት ነው፡፡ አይናቸው የተከፈተላቸው በቀላሉ የሚያዩትን በረከት እኛ ማየት ባለመቻላችን ብቻ ህይወታችን ውስን ከመሆኑም በላይ በክርስትና ህይወታችን መደሰት ያቅተናል፡፡ 
 
 
እውር ሰው አጠገቡ ያለውን መልካም ነገር ማየት እንደማይችል የልቦናችን አይኖቻችን ካልተከፈቱ በስተቀር እግዚአብሄር በክርስቶስ ያዘጋጀልንን በጎነትና ክብር ማየት ይሳነናል፡፡ 
 
 
እግዚአብሄር በክርስቶስ እየሱስ ለህይወትና እግዚአብሄርን ለመምሰል የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ ካዘጋጀልን በኋላ ባርከኝ የሚለው ጥያቄያችን አንዳንዴ ተገቢ አይደለም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የእኛ ችግር የበረከት እጥረት ሳይሆን በረከቱን የማየት የእይታ እጥረት ብቻ ነው፡፡ 
 
 
ስለዚህ ነው የመንፈስ አይናችን እየተከፈተ ሲሄድ ባርከኝ የሚለው ጥያቄያችን እየቀነሰ ለበረከት በሁሉ እጅግ ባለጠጎች መደረጋችንን ስላምናውቅ ፀሎታችብን ለበረከት አድርገኝ በሚለው የፀሎት ርእስ የሚሞላው፡፡ ስለዚህ ነው በእግዚአብሄር መንግስት ውስጥ ያለውን ተዝቆ የማያልቅ ሃብት ለማየት የልብ አይን መከፈት ወሳኝ ነው የሚባለው፡፡
 
 
ይህንን በክርስቶስ ያለውን አርነት ስናይ ብቻ ነው ክርስትናችንን በሚገባ የምናጣጥመው፡፡ 
 
 
ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡18-19
 
 
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ! 
 
 

No comments:

Post a Comment