Popular Posts

Monday, July 18, 2016

እየሱስ ይመጣል



የሰው ልጆች ሁሉ በሃጢያት ሃይል ስር ወድቀው ነበር፡፡ ሰዎች ሁሉ በሃጢያት ምክኒያት ለዘላለም ከእግዚአብሄር በተለያዩ ጊዜ የሃጢያታቸውን እዳ ለመክፈል በመስቀል ላይ ለመሞት እየሱስ ወደ ምድር ላይ መጥቶ ነበር፡፡ 

እየሱስ የሞትን ሃይል አሸንፎ ከሞት ተነስቶአል፡፡ በክብርም አርጎ በእግዚአብሄር ቀኝ ተቀምጦዋል፡፡ 

አሁን ዓመተ ምህረት ወይም የምህረት አመት ነው፡፡ ማንም ሰው ሃጢያተኝነቱን ተረድቶ ሀጢያቱ ለዘላለም ከእግዚአብሄር እንደሚለየው አውቆ ንስሃ ለመግባት መልካመ አጋጣሚ ነው፡፡ የሰው ልጆች ንስሃ እንዲገቡና እንዲመለሱ በመታገስ እየሱስ በሰማይ ቆይቶዋል፡፡ 

እየሱስ ዋጋ የከፈለው ዘርና ሃይማኖት ሳይለይ ለሰው ልጆች ሁሉ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሰውን ፊት አይቶ አያዳላም፡፡
ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው። 1 ጢሞቴዎስ 2፡4

እየሱስ በቅርብ ተመልሶ ይመጣል፡፡ 

እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ። ራእይ 22፡12

የሚገርመው ነገር ግን ተመልሶ የሚመጣው የሃጢያት እዳ ሊከፍል የሰው ልጆችን ሊያድን በድካም አይደለም፡፡ በቅርቡ ተመልሶ ሲመጣ በሃይልና በስልጣን ለእያንዳንዱም እንደ ስራው ሊከፍል በመላዕክት ታጅቦ ነው የሚመጣው፡፡ 

በቶሎ እመጣለሁ የሚለው ቃል እየሱስን ለሚከተል ሰው የሚያስፈነድቅ የምስራች ሲሆን እየሱስን ላልተቀበለ የሚያርበደብድ አስፈሪ መልዕክት ነው፡፡ 

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ያድርጉ! 




No comments:

Post a Comment