Popular Posts

Sunday, July 31, 2016

ከፊታችን ያሉ መልካም ቀኖች

እግዚአብሄር መልካም ነው፡፡ ለእኛ ለልጆቹ ሁል ጊዜ የተሻለ ነገር አለው፡፡ ከፊታችን እስከዛሬ ካየናቸው የተሻሉና መልካም ቀኖች እየመጡ ነው፡፡

እነዚህን መልካም ቀኖች ማየት የሚፈልግ ማድረግ ያለበት ነገሮች አሉ፡፡ መልካም ቀኖች ይመጣሉ ግን እነዚህን ቀኖች ማየትና አለማየት የእኛ ፋንታ ነው፡፡ በአንደበታችን የምናደርገው ነገር መልካሞቹን ቀኖች እንድናይ ወይም እንዳናይ ያደርጉናል፡፡

ህይወትን የሚወድና መልካሙንም ቀኖችን ማየት የሚፈልግ ሰው በንግግሩ መጠንቀቅ አለበት፡፡ ሰው እንደፈለገ እነደልቡ እየተናገረ መልካሞችን ቀኖች አያለው ማለት ዘበት ነው፡፡


ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ 1ኛ ጴጥሮስ 3፡10

ምክኒያቱም አንደበት እሳት ነው ፡፡ ካላግባብ ከተጠቀምንበት የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፡፡

አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ ያዕቆብ 3፡6


አንደበታችንን የማንገታ ከሆንን ሊረዳን ወደ እውነት ሁሉ ሊመራን የተሰጠንን ቅዱሱን የእግዚአብሄርን መንፈስ እናሳዝናለን፡፡

ሰው ራሱን ከመልካም ቀኖች ውድቅ ላለማድረግ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ሊከለክል ግዴታ ነው፡፡


ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ። ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ። ኤፌሶን 4፡29-30

ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ 1ኛ ጴጥሮስ 3፡10
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ


#ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #አንደበት #ምላስ #መልካምቀኖች #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment