Popular Posts

Sunday, July 17, 2016

ማኅፀን ገብቶ ይወለድ?

አንዳንድ ሰው የትም እንደማያመልጣቸው ሲናገሩና ሌላውን ሲያስፈራሩ የእናትህ ሆድ ተመልሰህ እንደምትገባ አይሃለሁ! ይላሉ፡፡ በመፅሃፍ ቅዱስም ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? የሚል ጥያቄ ያቀረበ ኒቆዲሞስ የሚባል ሃይማኖተኛ የአይሁድ አስተማተሪ ነበረ፡፡

ኒቆዲሞስ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው እየሱስ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም ስላለው ነበር፡፡

ምንም የኢትዮጲያን ብናውቅ ኢትዮጲያን ብንወድ ስለ ኢትዮጲያ ታሪክ አስተማሪ ብንሆን ነገር ግን ከኢትዮጲያዊ ካልተወለድን በስተቀር ወደዚህ ወደ ኢትዮጲያ ምድር መግባትና ኢትዮጲያዊ መሆን በፍፁም አንችልም፡፡

እንደዚሁ የእግዚአብሄርን መንግስት ብንፈልግ ስለ እግዚአብሄር መንግስት ታሪክ ብናውቅ ስለመንግስቱ ብናስተምር እንኳን የእግዚአብሄር መንግስት በመካከላችን ብትኖርም እንኳን ዳግመኛ ካልተወለድን በስተቀር ልናያትም ሆነ ልንገባባት እንችልም፡፡

ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው። ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ዮሐንስ 3፡3-5

ሰው ወደ ምድር ለመግባት ከእናቱና ከአባቱ መወለድ ግዴታው እንደሆነ ሁሉ ወደ እግዚአብሄር መንግስት ለመግባት ከውሃና ከመንፈስ መወለድ አለበት፡፡ እየሱስ በመስቀል ላይ የከፈለው የሃጢያት እዳ ለእኔ ነው ብሎ የተቀበለና እየሱስን የህይወቱ አዳኝና ጌታ እድርጎት የሾመ ሰው ሁሉ ዳግመኛ ከእግዚአብሄር ይወለዳል፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ ይሆናል ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም ይኖራል፡፡

ነገር ግን ሰው ከእናቱ እስከሚወለድ ድረስ ምድርን እንደማያያትና እንደማይገባባት ሁሉ እንዲሁ ሰው ምንም ሃይማኖተኛና መልካም ሰው ቢሆንም ዳግመኛ ካልተወለደ በስተቀር የእግዚአብሄርን መንግስትና ቤተሰብ ሊያያትም ሊገባባትም አይችል፡፡

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር ያድርጉ



No comments:

Post a Comment