Popular Posts

Tuesday, July 26, 2016

የኢየሱስ ስም

  • ከዘላለም ፍርድ የሚያድነው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት እንዲቀበል ነቢያት ሁሉ ይመሰክሩለታል። ሐዋርያት 10:43 ከሃጢያት ሊያድን የሚችለው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ። ማቴዎስ 1፡21 መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና። ሃዋሪያት 4፡12 በሰይጣን ላይ ስልጣን ያለው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
  • ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ዮሃንስ 1፡12 መሰበክ ያለበት የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ጽፎአል። ሉቃስ 24:47
በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ከስም ሁሉ በላይ ስልጣን ያለው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ፊልጵስዩስ 2፡9
  • ወደ እግዚአብሄር የምንቀርብት ብቸኛ ስም የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ። ዮሃንስ 15፡16
  • ለሚጠሩት ሁሉ ባለጠጋ የሆነ ስም የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤ ሮሜ 10፡12 ጉልበት ሁሉ የሚንበረከክለት የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ ፊልጵስዩስ 2፡10
  • በመፅሃፍ ቅዱስ የታዘዝነው የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በእየሱስ ስም አድርጉት ተብለን ነው፡፡
በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት። ቈላስይስ 3:17
 ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
 

No comments:

Post a Comment