Popular Posts

Thursday, July 21, 2016

የአእምሮ ገዳም

የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2
ሰዎች እግዚአብሄርን በመፈለጋቸውና ከዚህ አለም ነፃ ለመውጣት በመፈለጋቸው ከአለም መሸሽና ገዳም መግባት ይፈልጋሉ፡፡ ይህንንም ለማድረግ ገዳም ቢገቡም ጠልተውት የመጡት ክፉ የሃጢያት ሃሳብ ተከትሎዋቸው ይመጣል፡፡ በዚህም ምክኒያት ምንም ከከተማ ወጥተው ገዳም ቢገቡም የአለማዊነት አስተሳሰብ በአእምሮአቸው እስካለ ድረስ ከአለም መለየት ያቅታቸዋል፡፡ 
መፅሃፍ ቅዱስ አለምን ስለማንመስልበት ገዳም ይናገራል፡፡ ይህን አለም አለመምሰል የምንችለው ብቸኛው መንገድ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲታደስና የአለም ክፉ አስተሳሰብ በልባችን ቦታ ሳያገኝ ሲቀር ብቻ ነው ፡፡ 
አለማዊ የሚያደርገን ከተማ መኖራችን ወይም ከሰው ተለይተን አለመኖራችን ሳይሆን አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል አለመታደሱና ከሃጢያት ሃሳብ ጋር መኖራችን ነው፡፡ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲቃኝና ሲለወጥ በህይወታችን ለአለማዊነት ምንም ስፍራ አይኖርም፡፡
አለማዊ ከሚያደርገን ከሃጢያት ሃሳብ ጋር እስካለን ድረስ ከከተማ ወጥተን ከሰው ተለይተን ገዳምም ብንገባ ከሃጢያት ባርነት አናመልጥም፡፡ ምክኒያቱም አለማዊ ከሚያደርገን የሃጢያት ክፉ ሃሳብ አእምሮዋችን እስካልታደሰ ድረስ አለምን አለመምሰል አንችልም፡፡ 
ነገር ግን ባለንበት በስራችን በምንኖርበት ቦታ ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል አእምሮአችንን ካደስነው ይህን አለም ሳንመስል እግዚአብሄርን እያስደሰትን መኖርና ማገልገል እንችላለን፡፡

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ! 

No comments:

Post a Comment