Popular Posts

Saturday, July 2, 2016

ተጓደዱ



በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው።  እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። 1ኛ ዜና 16፡10-11

እግዚአብሄር መልካም አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር ይፈለጋል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ካልፈለገ ማንን ሊፈልግ ነው? እግዚአብሄር የሚፈለግ አምላክ ነው፡፡ 
 
ከሰማይ በታች ልናደርገው የሚገባ ከምንም ነገር እጅግ የሚሻልና የሚበልጥ ነገር እግዚአብሄርን መፈለግ ነው፡፡ ጊዜያችንን ጉልበታችንን ሁለንተናችንን ልናፈስበት የሚገባው እጅግ አትራፊ ነገር እግዚአብሄርን ሁልጊዜ መፈለግ ነው፡፡ 


በመፅሃፍ ቅዱስም እንድጓደድ ወይም እንድንመካ የተፈቀደልን አንድ ነገር እግዚአብሄርን መፈለጋችን ነው፡፡
ከሰማይ በታች ምንም የሚያስመካ ነገር የለም፡፡ እንዲያውም  ሰዎች በሚመኩበት ነገር እንዳንመካ እግዚአብሄር አስጠንቅቆዋል፡፡ 


እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ ኤርምያስ 9፡23

ነገር ግን የተፈቀደ ልንመካበት የምንችልበትና መመካት የሚገባን አንድ ነገር እግዚአብሄርን መፈለጋችን ነው፡፡ እግዚአብሄርን መፈለግ ባለጠግነትና ስኬት ነው፡፡ እግዚአብሄርን መፈለግ ሰላምና እርካታ ነው እግዚአብሄርን መፈለግ ደስታና ሙላት ነው፡፡ እግዚአብሄርን እንደመፈለግ የሚያፀናና የሚያስመካ ነገር የለም፡፡ 


ባለጠጎች ደኸዩ፥ ተራቡም፥ እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም። መዝሙር 34፡10


ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፦ ኤርምያስ 9፡24


እግዚአብሄርን መፈለግ ያስመካል፡፡ በሌላ በምንም ነገር አትመካ ነገር ግን እግዚአብሄርን በመፈለግህ ተደድ ደስ ይበልህ ተመካ፡፡ 


በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው።  እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። 1ኛ ዜና 16፡10-11


No comments:

Post a Comment