Popular Posts

Sunday, July 3, 2016

ክብርህን ሳይ እጠግባለሁ

እግዚአብሄርን ማምለክ ከሰማይ በታች እጅግ ልዩ ልምምድ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ማየት እጅግ ያስደስታል፡፡ በእግዚአብሄር ክብርና መልካምነት መዋጥ መረስረስ መወሰድ የመጨረሻው ልምምድ ነው፡፡ ይህ ልምምድ በምድር ላይ ካሉ የሚያስደስቱ ልምምዶች እጅግ ይለያል፡፡ እግዚአብሄርን ማምለክ ከምንም ጋር የሚወዳደር አይደለም፡፡

ጌታን እየሱስን የሚወዱ ክርስቲያኖች ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ። አልፋና ዖሜጋ አንተ ነህ፡፡ አንተንና አንተን ብቻ እናመልካለን ይሉታል፡፡ ራእይ 1፡8

ስለዚህ ነው መዝሙረኛው ወደ እግዚአብሄር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ የሚለው እግዚአብሄርን በክብሩ ማየት ስለወደደ ነው፡፡ መዝሙር 122፡1

በእግዚአብሄር መገኘት የዘላለም ደስታና ፍስሃ አለ፡፡ እግዚአብሄርን ማምለክ ያድሳል ያለመልማል፡፡

የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ። መዝሙር 16፡11

እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ፤ ክብርህን ሳይ እጠግባለሁ። መዝሙር 16፡15

እግዚአብሄርን ስናለምልክ የራሳችንን ድካም እንረሳለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመልክ በእግዚአብሄር ሃይል እንታደሳለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመለክ በጨለማ ውስጥ ብርሃንን እናያለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመለክ በእግዚአብሄር መልካምነት እንወሰዳለን እንማካለን እንረሰርሳለን፡፡

እግዚአብሄርን በውበቱ ስናየው ማስተዋሉ በማይመረመር በእግዚአብሄር እውቀት እርፍ እንላለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመልክ ተስፋችን ይለመልማል፡፡ እግዚአብሄርን ስናመልክ ራሳችንንና የከበቡንን ነገሮች እንረሳለን፡፡

ዓይኖችህ ንጉሥን በውበቱ ያዩታል፤ እነርሱም በሩቅ ያለች ምድርን ያዩአታል። ኢሳይያስ 33፡17
አምላካችሁንም እግዚአብሔርን ታመልኩታላችሁ፥ እርሱም እህልህንና ውኃህን ይባርካል፤ በሽታንም ከመካከልህ አርቃለሁ። ዘጸአት 23፡25

አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ። ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ። መዝሙር 63፡1-2

No comments:

Post a Comment