Popular Posts

Tuesday, July 12, 2016

የትኛው ጥበብ ?

በህይወት ለመከናወን ጥበብ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ በህይወት ምን ማድረግ እንዳለብን ግራ በሚገባን ጊዜ ምን ማድረግ እንዳለብን የሚያሳየን ጥበብ ነው፡፡

ጥበብ ሁሉ ግን መልካም ጥበብ አይደለም፡፡ የሚገነባ ጥበብ አለ የሚያፈርስ ደግሞ ጥበብ ደግሞ አለ፡፡ ሰው ጥበብ አለው ማለት ከላይ ከእግዚአብሄር የተቀበለው ነው ማለት አይደለም፡፡ አንዳንዴ እነዚህን ከእግዚአብሄር የሆነውንና ከሰይጣን የሆነውን የጥበብ አይነቶች ለመለየት እንቸገራለን፡፡

መፅሃፍ ቅዱስ የእነዚህ እጅግ የተያዪ የጥበብ አይነቶች ባህሪያቸውና የሚለዩበትን ምልከቶች ያስተምረናል፡፡ ጥበብ ብለን እየኖርን ያለንበትን እንድንፈርትሽና ከላይ ያልሆነውን ጥበብ በፍጥነት እንድንጥል የላይኛይቱን ጥበብ በየዋህነት በኑሮዋችን እንድናሳይ ይመክራል፡፡

ከላይ ከእግዚአብሄር የምንቀበለውና የምድር የስጋና የአጋንንት ጥበብ ባህሪያቸውንና ምልክታቸውን መፅሃፍ ይዘረዝራል፡፡

ላይኛይቱ የእግዚአብሄር ጥበብ

ንፅህት- ከልብ ንፅህና ከክፉ ሃሳብ የሌለባት
ታራቂ- ርሁርጉ ሰላምን የምትፈልግ ለአንድነት የምትተጋ
እሺ ባይ - ትሁት ታዛዥ አገልጋይ
ምህረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፡ ምህረትን የምትወድ
ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት- የምትታመን፡ የማታስመስል

የምድር የስጋ የአጋንንት ጥበብ

መራርነት - ይቅር የማትል ፡ የማትተው
ቅንአት- የሌላው መልካምነት እረፍት የሚነሳት
አድመኝነት - ለራስ ጥቅም ሰዎችን ለክፋት የሚያነሳሳ
ሁከትና ክፉ ስራ - ረብሻን የሚወድ 
 
ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ። ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ፥ አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ። ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፤ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው፥ የአጋንንትም ነው፤ ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና። ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፥ በኋላም ታራቂ፥ ገር፥ እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት። ያዕቆብ 3፡13-17

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

No comments:

Post a Comment