Popular Posts

Sunday, August 27, 2023

ወንጌልን የሚሰብኩ ከወንጌል ቀለብ እንዲቀበሉ ጌታ ደንግጎአል ክፍል 6

 


ወንጌልን የሚሰብኩ ከወንጌል ቀለብ እንዲቀበሉ ጌታ ደንግጎአል ክፍል 6

ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግንአስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።የማቴዎስ ወንጌል 632-33

ክርስቶስ ኢየሱስን የምንከተል ሁላችን በህይወት የመጀመሪያው ስራችን የእግዚአብሔርን ፅድቅናመንግስቱን መከተል ነው፡፡ 

ለእኛ ለእግዚአብሔር ልጆች ስለምንበላው ስለምንለብሰው መጨነቅ አይመጥነንም፡፡ ይልቁንምትኩረታችን መሆን ያለበት የእግዚአብሔር  መንግስት ጥቅም መጠበቅ እና በመንግስቱ መስፋት ላይነው፡፡ 

የሰው አገልግሎት ሊከፍል የሚችል የገንዘብ መጠን የለም፡፡ ሰው የሚከፈለው ስለአገልግሎቱ ሳይሆንበምድር ላይ ለመኖር ስለሚያስፈልገው ወጪ ብቻ ነው፡፡ 

ሰው ስለአገልግሎቱ የሚከፈለው በእግዚአብሐር ብቻ ነው:: 

በተለይ የወንጌል አገልጋይ እግዚአብሔር ፍላጎቴን የሚያሟላው የእርሱ ልጅ ስለሆንኩኝ ብቻ ነውብሎ ማመን አለበት፡፡ ወንጌልን የሚሰራ የሚያገለግለው ህዝብ እንደሚገባው ባይንከባከበው እንኳንእግዚአብሔር ጉድለቱን እንደሚሸፍን በእግዚአብሔር አሰራር መታመን አለበት፡፡ 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

#ኢየሱስ #ጌታ #ገንዘብ #ቀለብ #ወንጌል #ኑሮ #ስጡ #ቤተክርስቲያን #መፅሐፍቅዱስ #ቃል#እግዚአብሔር #ገቢ


No comments:

Post a Comment