Popular Posts

Wednesday, August 23, 2023

ወንጌልን የሚሰብኩ ከወንጌል ቀለብ እንዲቀበሉ ጌታ ደንግጎአል ክፍል 2

 

እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆንን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን? 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡11

አብዛኛው ጊዜያቸውን መንፈሳዊውን ነገር በመዝራት የሚያሳልፉ አገልጋዮች መንፈሳዊ ነገር ከሚዘሩባቸው አገልጋዮች ስጋዊውን ነገር ቢያጭዱ እንግዳ ነገር አይደለም፡፡

እነዚህ አገልጋዮች አብዛኛውን ጊዜያቸውን በፀሎት እና በቃሉ አገልግሎት የሚተጉ አገልጋዮቻችን ናቸው፡፡

መንፈሳዊ ነገር የሚዘራበት ሰው ሁሉ አብዛኛውን ጊዜያቸውን መንፈሳዊውን ነገር ለመዝራት የሰጡትን አገልጋዮች በስጋዊ ነገር የመንከባከብ ሃላፊነት አለበት፡፡

መንፈሳውን ነገር የሚዘሩ አገልጋዮች በሚያገለግሏቸው ሰዎች ስጋዊ ፍላጎታቸው ካልተሸፈነ በስተቀር ለፀሎት እና ለቃሉ የሚተጉ አገልጋዮችን ማግኘት አይቻልም፡፡

በህይወቱ ላይ ለሚዘራው ለመንፈሳዊው ነገር አክብሮት ያለው ማንኛውም ሰው ስጋዊውን ነገር ለማካፈል ወደኋላ አይልም፡፡

በህይወቱ ላይ መንፈሳዊውን ነገር ለሚዘሩ አገልጋዮች እውቅና የሚሰጥ ማንኛውም ሰው ስጋዊ ነገርን መዝራቱ እንደ ትክክለኛ ነገር እንጂ እንደ እንግዳ ነገር አይመለከተውም፡፡

ቤተክርስትያን የምታድገው እና የምታሸንፈው እነዚህ ለቤተክርስትያን የተሰጡ አገልጋዮች ለፀሎት እና ለቃል እንዲተጉ በስጋዊ ነገራቸው ላይ የሚዘራ የቅዱሳን ህብረት ሲኖር ብቻ ነው፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

#ኢየሱስ #ጌታ #ገንዘብ #ቀለብ #ወንጌል #ኑሮ #ስጡ #ቤተክርስቲያን #መፅሐፍቅዱስ #ቃል #እግዚአብሔር #ገቢ


No comments:

Post a Comment