Popular Posts

Tuesday, August 29, 2023

በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል ክፍል 1

 

በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል . . . እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ትንቢተ ኢሳይያስ 53፡4-5

ኢየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ዋጋ ከፍሎዋል፡፡ ነፍሳችን ከሃጢያት እስራት እንድትድን ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሚያስፈልገውን ቅጣት ሁሉ በመቀጣት ሃጢያታችንን ወስዶዋል፡፡

እንዲሁም ኢየሱስ ስለ ህመማችን እንዲሁ በመስቀል ላይ ዋጋ ከፍሎዋል፡፡ ኢየሱስ ደዌያችንን በመስቀል ላይ ተሸክሞዋል፡፡

ኢየሱስ ስለ ሐጢያታችን በመስቀል ላይ ዋጋ በመክፈሉ የተነሳ በሃጢያት መኖር እንደሌለብን ሁሉ ኢየሱስ ስለ ፈውሳችን ስለተገረፈ በደዌ መኖር የለብንም፡፡

ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ #በመገረፉ #ቁስል #ተፈወሳችሁ። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፡24

የነፍሳችን መዳን የመቤዠታችን ክፍል እንደሆነ ሁሉ የስጋ ፈውስ የመቤዠታችን አንዱ አካል ነው፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

#ኢየሱስ #ጌታ #ህማም #ደዌ #ወንጌል #ፈውስ #ጤንነት #ቤተክርስቲያን #መፅሐፍቅዱስ #ቃል #እግዚአብሔር #መስቀል


No comments:

Post a Comment