Popular Posts

Friday, June 30, 2023

ከፈለግን እና ከተዘጋጀን እንሰማዋለን


እግዚአብሔር አምላካችን ነው፡፡ እኛ ለክብሩ የፈጠረን የእርሱ ህዝቦች ነን፡፡ እግዚአብሔር እንድንፈለገው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔርን ስንፈልገው ደስ ይለዋል፡፡ እግዚአብሔር እርሱን ለመስማት ጆሮዋችንን እንድናዘነበል ይፈልጋል፡፡

እግዚአብሔርን በእውነት ከፈለግነው ይገኝልናል፡፡ እግዚአብሔር ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም፡፡

እኛ እግዚአብሔርን መስማት ከምንፈልገው በላይ እርሱ በእኛ እንዲሰማ ይፈልጋል፡፡ እኛ ለህይወታችን ካለን አላማ በላይ ለእኛ የተሻለ አላማ አለው፡፡

ፈቃዱን ለማድረግ የምንወድ ከሆንን የእርሱን ፈቃድ እንረዳለን፡፡ ምክኒያቱም እግዚአብሔር ከተናገረ እኛ እንሰማለን፡፡ ፈቃዱን ለማድረግ እየወደድን እርሱን አለመስማት የማይታሰብ ነገር ነው፡፡

ፈቃዱን ሊያደርግ የሚወድ ቢኖር፥ . . . ያውቃል። የዮሃንስ ወንጌል 7፡17

እግዚአብሔር መንገዳችን እንዲቀና ይፈልጋል፡፡ እርሱን ለመስማት ራሳችንን ከሰጠን መንገዳችን ሁሉ ቀና ይሆናል፡፡

በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። መጽሐፈ ምሳሌ 3፡5-6

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

 

No comments:

Post a Comment