Popular Posts

Wednesday, June 21, 2023

በእግዚአብሔር ቃል ከባቢ ድምፁን መስማት

 


እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር ቢናገርም ሰው ድምፁን ለመስማት ራሱ ካላዘጋጀ በእግዚአብሔር ምሪት ተጠቃሚ አይሆንም፡፡

ታዲያ የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመለየት ከሚጠቅሙ ከባቢዎች መካከል የእግዚአብሔርን ቃል መሰላሰል አንዱ እና ዋነኛው ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰል የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመለየት ያስችለናል፡፡

ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ እያሰብን እና እያሰላሰልን የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመለየት መቻል ዘበት ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰላችን የእግዚአብሔርን ድምፅ የመስማት እና የመለየት እድላችንን በእጅጉ ከፍ ያደርገዋል፡፡ 

የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰላችን የእግዚአብሔርን ድምፅ የመለየት አቅማችንን ከፍ ከማድረጉ በተጨማሪ የሰማነውን ድምፅ እንድንተገብረው አቅምን ይሰጠናል፡፡

የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 1፡8

እግዚአብሔር በቃሉ በኩል ይናገረናል፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ ከመናገሩ በተጨማሪ የእግዚአብሔርን ቃል ስናሰላስል የእግዚአብሄርን ድምፅ እንድንለይ ከባቢያችንን የተመቻቸ ያደርገዋል፡፡  

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


No comments:

Post a Comment