Popular Posts

Saturday, June 24, 2023

አእምሮን በማደስ የእግዚአብሔርን ድምፅ መስማት

 

የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ወደ ሮሜ ሰዎች 12፡1

እግዚአብሔር ከመናገር አቋርጦ አያውቅም፡፡ የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመለየት ከሚጠቅሙን ነገሮች አንዱ በቃሉ አእምሮዋችንን ማደስ ነው፡፡

የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስብ እንደ እግዚአብሔር ያስባል ይባላል፡፡ የእግዚአብሔር ድምፅ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር አብሮ ይሄዳል፡፡ የእግዚአብሔር ድምፅ በቃሉ ከታደሰው አእምሮ ጋር ይስማማል፡፡

አእምሮዋችን በቃሉ ሲታደስ የምንሰማውን የእግዚአብሔርን ድምፅ በቀላሉ መለየት እንችላን፡፡ በእግዚአብሔርን ቃል አእምሮን ማደስ ከቃሉ ጋር አብሮ የሚሄደውን ድምፅ ለመለየት ያስችለናል፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


No comments:

Post a Comment