Popular Posts

Friday, June 16, 2023

ክርስቶስ በእኔ ይኖራል

 


ክርስቶስ ኢየሱስን እንደአዳኛችን የተቀበልን ሁላችን በመንፈሱ አማካኝነት ክርስቶስ በውስጣችን ይኖራል፡፡ ይህ መለኮታዊ ህይወት በውስጣችን መኖር ያስፈለገው ምክኒያቱ እንዲመራን እና እግዚአብሄር በምድር ላይ እንድንፈፅመው የሰጠንን ስራ እንድናከናውን እንዲያስተምረን ነው፡፡

በውስጣችን ያለው መለኮታዊ ህይወት አንድን ነገር ማሰብ ሲፈልግ አብረነው እናስባለን ፣ መናገር ሲፈልግ አብረነው እንናገራለን ፣ ዝም ማለት ሲፈልግ አብረነው ዝም እንላለን መሄድ ሲፈልግ አብረነው አንሄዳለን ፣ መቀመጥ ሲፈልግ አብረነው እንቀመጣለን፡፡ በአጠቃላይ በውስጣችን ለሚኖረው ኢየሱስ አይን እግር እጅ አፍ እንሆንለታለን፡፡

ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው። ወደ ገላትያ ሰዎች 2፡20

ይህን በውስጣችን የሚኖረውን የእግዚአብሄርን ህይወት ከሰማን በሰላም ወደ መዳረሻችን እንደርሳለን፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


No comments:

Post a Comment