Popular Posts

Tuesday, June 27, 2023

ድምፅ ከእግዚአብሔር እንዳልሆነ የምናውቀው

 


ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል። እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና። ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህ፦ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋል አልሁ። የዮሐንስ ወንጌል 16፡13-15

መንፈስ ቅዱስ ሊመራን ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ አዳኝ በተቀበልን በእኛ ውስጥ ይኖራል፡፡ የመንፈስ ቅዱስን ምሪት የምንለየው ክርስቶስን በማክበሩ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ እንኳን ሌላውን ሰው ሊያከብር ይቅርና እራሱን እንኳን አያከብርም፡፡ መንፈስ ቅዱስ እኛን በመምራት ክርስቶስን ሊያከብር በእኛ ውስጥ አለ፡፡

የመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንዳልሆነ የምናውቅው ታዲያ የምንሰማው ድምፅ ክርስቶስን በማክበሩ እና ባለማክበሩ ነው፡፡ ክርስቶስን ካላከበረ በፋንታው ሰውን የሚያከብር ከሆነ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት አይደለም፡፡

መንፈስ ቅዱስ ሲናገር ለሰው ጥቅም ለክርስቶስ ክብር ነው፡፡ ክርስቶስን የሚሸፍን ሰውን የሚያሳይ ነገር ከመንፈስ ቅዱስ አይደለም፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


No comments:

Post a Comment