Popular Posts

Tuesday, June 20, 2023

ድምፁን ለመስማት የሚጠቅም የፀጥታ ከባቢ

 

እግዚአብሔር ይናገራል፡፡ መናገር የእግዚአብሔር ሃላፊነት ነው፡፡ መስማት ደግሞ የሰው ሀላፊነት ነው፡፡ ሰው እግዚአብሔርን ለመስማት ራሱን ማዘጋጀት አለበት፡፡

ራሳችንን በሚገባ በማዘጋጀት በአለም ላይ መስማት ከሚፈልጉ ከብዙ ድምፆች መካካል የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመስማት ራሳችንን መለየት ይገባናል፡፡

ልጄ ሆይ፥ ንግግሬን አድምጥ ወደ ቃሌም ጆሮህን አዘንብል። መጽሐፈ ምሳሌ 4፡20

የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመለየት ለእግዚአብሔር ጊዜ መስጠት እና ድምፁን ለመስማት መለማመድ ይጠይቃል፡፡ ኢየሱስ ስትፀልይ በርህን ዝጋ ያለው ስለዚህ ነው፡፡ ስንፀልይ እግዚአብሄርን ለመስማት ወዲህ እና ወዲያ የሚወስደንን አሳባችንን ዝም ማሰኘት ይጠይቃል፡፡ 

አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል። የማቴዎስ ወንጌል 6፡6

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


No comments:

Post a Comment