Popular Posts

Monday, June 26, 2023

እግዚአብሄርን ከመስማት የሚያግዱን ነገሮች


እግዚአብሄር ሁልጊዜ መናገር ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ሊናገረን ብሎም ወዳሰበልን መዳረሻ ሊመራን ይፈልጋል፡፡ የእግዚአብሄር መፈለግ ግን በቂ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ነገር የእግዚአብሄርም የሰው የቅንጅት ስራ እንደመሆኑ መጠን እግዚአብሄር ቢናገርም እኛ ካልሰማን የትም አንደረስም፡፡

እግዚአብሄርን ከመስማት ከሚያግዱን ነገሮች አንዱ ፈቃዱን ለማድረግ አለመራብ እና አለመጠማት ነው፡፡

ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና። የማቴዎስ ወንጌል 5፡6

ፈቃዱን ለማድረግ ብርቱ ፍላጎት ካለን እግዚአብሄርን ለመስማት የሚያስችለንን ምቹ ሁኔታ እናመቻቻለን፡፡

ሌላው እግዚአብሄርን በመስማት ሙሉ ፍሬ እንዳናፈራ የሚያደርገን ለኑሮ ጭንቀት ፊት መስጠ ነው፡፡ ለኑሮ ሃሳብ እና ለባለጠግነት ምኞት ፊት ከሰጠነው በቁማችን ሊውጠን የሚችል አደገኛ ነገር ነው፡፡

በእሾህ መካከልም የወደቀ እነዚህ የሚሰሙት ናቸው፤ መንገዳቸውንም ሄደው በሕይወት ዘመን በአሳብና በባለ ጠግነት ምቾት ይታነቃሉ፥ ሙሉ ፍሬም አያፈሩም። የሉቃስ ወንጌል 8፡14

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


 

No comments:

Post a Comment