Popular Posts

Sunday, June 18, 2023

እግዚአብሔር እረኛ

 


እግዚአብሔር እረኛችን ነው፡፡ እግዚአብሔር ይመራናል፡፡ የእግዚአብሔርን ምሪት ከተከተለን በህይወታችን የምናጣው ምንም መልካም ነገር የለም፡፡ 

እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። መዝሙረ ዳዊት 23፡1-3

እርሱ አምላካችን ነውና፥ እኛ የማሰማርያው ሕዝብ የእጁም በጎች ነንና። መዝሙረ ዳዊት 95፡7

እግዚአብሄርን የመሰለ ማስተዋሉ የማይመረመር እረኛ እያለን እረኛ እንደሌላቸው በጎች አንቅበዝበዝ፡፡ ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሄር እረኛችን ሆኖ በትህትና እንከተለው እንጂ ወደገዛ መንገዳችን አናዘንብል፡፡ ይልቁንም ወደነፍሳችን እረኛ እና ጠባቂ እንመለስ፡፡ 

እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፡25

እግዚአብሔርን እንደ እረኛ ሁልጊዜ እውቅና እንስጠው፡፡ 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

No comments:

Post a Comment