Popular Posts

Thursday, June 15, 2023

የህይወት መንፈስ ህግ ወይስ ክፉና ደጉን የምታስታውቀው ፍሬ

 



እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጠር በየዋህነት እርሱን እንሰዲከተለው ፈጠረው፡፡ ሰው ይህ ክፉ ነው ይህ መልካም ነው ብሎ መለየት አልነበረበትም፡፡ የሰው ብቸኛ ድርሻ እግዚአብሔርን  በየዋህነት ማመን እና መከተል ብቻ ነበር፡፡

አሁንም እግዚአብሄር በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንጂ ክፉውንና ደጕን በምታስታውቀው ፍሬ እንድንኖር አይፈለግም፡፡ ሰው በውስን አእምሮው አስቦ ክፉ የሚለው ሁሉ ክፉ አይደለም ሰው መልካም የሚለው ሁሉ መልካም አይደለም፡፡

እግዚአብሄር መልካም ነው ካለው ብቻ መልካም ነው እግዚአብሄር ክፉ ነው ካለው ብቻ ክፉ ነው፡፡

እግዚአብሄር በመንገዳችን ሁሉ ለእርሱ ምሪት እውቅና እንድንሰጥ እንጂ በራሳችን ማስተዋል እንድንደገፍ አይፈልግም፡፡

በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። መጽሐፈ ምሳሌ 3፡5-6

ሰው መልካም የሚለውም እንኳን የእግዚአብሄር ፈቃድ ላይሆን ይችላል፡፡

ይልቁንም የአእምሮዋችንን ጫጫታ ዝም አሰኝተን በልባችን ባለው በህይወት መንፈስ ህግ ስንመራ ብቻ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈፀም እንችላልን፡፡

በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡2

ከክፉና ደግ ምርጫ ነፃ የምንወጣው በውስጣችን የሚኖረውን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን የህይወት መንፈስን ህግ ስንከተል ብቻ ነው፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


No comments:

Post a Comment