Popular Posts

Saturday, April 28, 2018

ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ

መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ። ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ማቴዎስ 22፡36-38
እግዚአብሄር ለክብሩ ፈጥሮናል፡፡
እግዚአብሄር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን ለአላማው ነው፡፡
እግዚአብሄር ከምንም ነገር በፊት እንድናስቀድመው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከምንም ነገር በላይ እንድንሰማው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከምንም ነገር በላይ እንድንፈልገው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከምንም ነገር በላይ እንድንፈራው ይፈልጋል፡፡
ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁአችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን። 1ኛ ጴጥሮስ 3፡15
እግዚአብሄር ከራሳችን በላይ እንድንወደው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ራሳችንን ከእርሱ እንድናስቀድም አያስፈልግም፡፡ እግዚአብሄር ስለእርሱ ነፍሳችንን እንድንክድ ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከደስታችን በላይ እንድንወደው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከምኞታችን በላይ እንድናስቀድመው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከፍላጎታችን በላይ እንድንወደው ይፈልጋል፡፡
ማንም ወደ እኔ የሚመጣ ቢኖር አባቱንና እናቱን ሚስቱንም ልጆቹንም ወንድሞቹንም እኅቶቹንም የራሱን ሕይወት ስንኳ ሳይቀር ባይጠላ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም። ሉቃስ 14፡26
እግዚአብሄር በህይወታችን ሁለተኛ መሆን አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ከሌላ ነገር ጋር መዳበል አይፈልግም፡፡
ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ማቴዎስ 10፡37
እግዚአብሄር ከምንም ነገር በላይ እንድናስቀድመው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ከምንም ነገር በላይ እንድንወደው ይፈልጋል፡፡
መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ። ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ማቴዎስ 22፡36-38
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ፍቅር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #በፍፁምልብ #በፍፁምሃሳብ #በፍፁምነፍስ #በፍፁምሃይል #መውደድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment