Popular Posts

Sunday, April 22, 2018

ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ

በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። መዝሙር 91፡1
በዚህ ለህይወታችን ምንም ማስተማመኛ በሌለው አለም በአግዚአብሄር ጥበቃ እንደመታመን የሚያሳርፍ ነገር የለም፡፡ አለ ያልነው ሰው በድንገት ሲወሰድ ደጋግመን አይተናል፡፡ ይሞታል ብለን በአእምሮዋችን ያላሰብነው ሰው ሲሞት አይተናል፡፡
ያልታሰቡ አደጋዎችን ስናይ እኔስ መድህኔ ምንድነው ብለን እንጠይቃለን፡፡ ለህይወታችን ብቸኛ ጥበቃ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡ እስካሁንም ችለን ራሳችንን አልጠበቅንም፡፡ እስካሁንም የጠበቀን እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡  
ካላየነውና ካየነው ክፋት እስጥሎና ከልሎ እዚህ አድርሶናል፡፡ እግዚአብሄር ሳናየው ያስመለጠንን አደጋ ሁሉ ብናይ ከማሰብና ከመያዝ አቅማችን በላይ ስለሆነ አእምሮዋችን ጤነኛ የሚሆን አይመስለኝም፡፡
ከክፉ አደጋ ተጠብቀን በህይወት በመኖራችን ብቻ እግዚአብሄር ሊመሰገን ይገባዋል፡፡ እግዚአብሄርን ለማመስገን ህያው መሆናችን መተንፈሳችን ብቻ ይበቃል፡፡
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን፦ ሃሌ ሉያ። መዝሙር 150፡6
አንዳንድ አደጋዎችን ስንሰማ ከአልጋችን ተነሰተን እንደገና ህይወትን መጋፈጥ ይፈታተነናል፡፡ ስለ ደህንነታችን ስናስብ እንደገና መኖር እንፈራለን፡፡ እግዚአብሄርን ካላሰብን በስተቀር እንደገና ለመኖር አቅም እናጣለን፡፡
በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። እግዚአብሔርን፦ አንተ መታመኛዬ ነህ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ። እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና። በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል። ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥ በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም። በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም። በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ። መዝሙር 91፡1-8
የትኛውም ብልጠታችን ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥ በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አይጠብቀንም፡፡ የትኛውም እውቀታችን ከአዳኝ ወጥመድና ከሚያስደነገጥ ነገር አያድነንም፡፡
ያለው ብቸኛ አማራጭ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡ ያለው አማራጭ በልኡል መጠጊያ መኖር ነው፡፡ አንዱና ብቻኛው አማራጭ ከላባዎቹ በታች በጋረደን በእግዚአብሄር ክንፎች መተማመን ነው፡፡
በእግዚአብሄር ካልታመንን የምንታመንበት ምንም ነገር አይቀርልንም፡፡ ሁሉን በሚችል አምላክ መታመን አማራጭ አይደለም፡፡ በምድር ላይ ስለደህንነታችን ሁሉን በሚችል በእግዚአብሄር መታመን ግዴታ ነው፡፡
ትእዛዙ በፍፁም ልብህ በእግዚአብሄር ታመን ነው፡፡ በፍፁም ልብህ በእግዚአብሄር ታመን። ምሳሌ 3፡5
ትእዛዙ በእግዚአብሄር ታመን በምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ ነው፡፡
በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። መዝሙር 37፡3
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መደገፍ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment