Popular Posts

Sunday, April 29, 2018

የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል

ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝሙር 1፡2-3
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው እርሱን እንዲያመልከውና እንዲታዘዘው ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ቃሉን እንዲሰማና እንዲያደርግ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በቃሉ አንዲኖር ነው፡፡
እግዚአብሄር በሌላ ነገር ሳይሆን በቃሉ ደስ የሚሰኝን ሰው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ሌላን ነገር ሳይሆን ቃሉን የሚሰማን ሰው ይፈልጋል፡፡
አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም ኃይልህ ውደድ። እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ። ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥ ስትነሣም ተጫወተው። በእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረው፤ በዓይኖችህም መካከል እንደክታብ ይሁንልህ። በቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈው። ዘዳግም 6፡5-9    
እግዚአብሄር ሌላ ነገርን ሳይሆን ቃሉን የሚያስብን ሰው ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ቃሉን በቀንና በሌሊት የሚያሰብን ሰው ይፈልጋል፡፡
በረከትና ስኬት ያለው በእግዚአብሄር ቃል ውስጥ ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስናሰላስል እና ስናደርገው ህይወታችን ፈፅሞ ይለወጣል፡፡
የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። ኢያሱ 1፡8
የእግዚአብሄርን ቃል የሚያሰላስልና የሚያደርግ ሰው እግዚአብሄር ሁልጊዜ ከእርሱ ጋር ይሆናል፡፡ እግዚአብሄር ሙሉ ለሙሉ የተሳካ እንደሆነ ሁሉ የእግዚአብሄርን ቃል የሚያስብና የሚያደርግ ስው በሚሰራው ሁሉ ይከናወናል፡፡
ይህንን ፅሁፍ ሼር ማድረግ ቢወዱ 
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes 

#ቃል #ምስጉን #ሃሳብ #ማሰላሰል #ወንጌል #ደቀመዝሙር #ኢየሱስ #ጌታ #መዳን #አማርኛ #ኢትዮጲያ #አቢይዋቁማ #አቢይ #አቢይዋቁማዲንሳ #ስኬት #ክንውን ###ፌስቡክ #አዋጅ   

No comments:

Post a Comment