Popular Posts

Saturday, December 9, 2017

ኢየሱስ በመካከላችን እንዲገኝ የሚያደርገው

ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና። ማቴዎስ 16፡18-20
የእግዚአብሄርን የመዳኛ መንገድ ኢየሱስን የተቀበሉ ሁሉ በምድር ላይ የእግዚአብሄር ተወካዮች ናቸው፡፡ ኢየሱስን የተቀበሉ ሁሉ ኢየሱስ በምድር ላይ መስራት የጀመረውን የእግዚአብሄርን መንግስት ስራ ሊፈፅሙ በምድር ላይ የተሾሙ የእግዚአብሄር ተወካዮች ናቸው፡፡  
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡12
እግዚአብሄር በሰማይ እንዳለ ሁሉ ቅዱሳን በምድር ላይ ላይ ናቸው፡፡ በክርስቶስ ያመኑ የእግዚአብሄር ልጆች በሰማይ ያለው የእግዚአብሄር አምባሳደሮች ናቸው፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች የእግዚአብሄርን ፈቃድ በምድር የሚያስፈፅሙ የኢየሱስ ተወካዮች ናቸው፡፡
አማኞች ሲሰበሰቡ ለአንድ አላማ መስበሰብ አለባቸው፡፡ አላማ የሌለው መሰባሰብ ከግብ አያደርስም፡፡ ለመሰብሰብ ብቻ የሆነ መሰብሰብ ውጤት አያመጣም፡፡ መሰብሰባችን አንድ የጋራ አላማን ይጠይቃል፡፡
እያንዳንዳችን በየራሳችን የግል አላማ ሳይሆን በአንድ አላማ መሰብሰብ ይኖርብናል፡፡ የመሰብሰባችን አላማ የኢየሱስ ስም መሆን አለበት፡፡ ስንሰበሰብ በኢየሱስ ስም ልንሰበሰብ ይገባል፡፡ የሚያሰባስበን የኢየሱስ ስራ ፣ የኢየሱስ ተልእኮና የኢየሱስ ስም መሆን አለበት፡፡ የምንስበሰበው ኢየሱስ በምድር ላይ መስራት የጀመረውን ለመጨረስ ኢየሱስን ወክለን የእግዚአብሄርን መንግስት ስራ ለመፈፀም ሊሆን ይገባዋል፡፡
ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ኢየሱስ የመረጣቸውን ሐዋርያትን በመንፈስ ቅዱስ ካዘዛቸው በኋላ እስከ ዐረገበት ቀን ድረስ፥ ያደርገውና ያስተምረው ዘንድ ስለ ጀመረው ሁሉ መጀመሪያውን ነገር ጻፍሁ፤ ሐዋርያት 1፡1-2
የምንሰበሰበው ኢየሱስ በምድር ላይ ሰርተን እንድፈፅመው የላከንን ስራ ለመስራት መሆን አለበት፡፡ የምንሰበሰበው ኢየሱስን ወክለን መሆን አለበት፡፡ የምንሰበሰበው አብ ኢየሱስ እንደላከው ኢየሱስ የላከንን ተልእኮ ለመፈፀም መሆን አለበት፡፡   
ኢየሱስም ዳግመኛ፦ ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እንደ ላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኋለሁ አላቸው። ዮሃንስ 20፡21
ኢየሱስን ወክለን የእግዚአብሄርን መንግስት ለመስራት ባለ አንድ አላማ ከተሰበሰበን ኢየሱስ በመካከላችን ይገኛል፡፡ ለእግዚአብሄር መንግስት አላማና ኢየሱስን ወክለን ስንሰበሰብ ኢየሱስ በመካከላችን አንዲገኝ መለመንና መጨቅጨቅም እሰከማያስፈልገን ድረስ እንደቃሉ በቃሉ በመካከላችን ይገኛል፡፡ ኢየሱስ በመካከላችን የሚገኘው በእርሱ ቦታ ሆነንና እርሱን ወክለን የእግዚአብሄርን መንግስት ጥቅም ለማስከበርና መንግስቱን ለማስፋት የምንለምነውን ሁሉ አብ እንዲያደርገው ነው፡፡ በኢየሱስ ስም ስንሰበሰብ በመካከላችን የሚገኘው ስለ እያንዳንዳችን የግል ጥቅም ሳይሆን በአጠቃላይ ስለ እግዚአብሄር መንግስት ጥቅም ነው፡፡
ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና። ማቴዎስ 16፡18-20
በኢየሱስ ስም ከተሰበሰብን መገኘቱ ይሰማንም አይሰማንም ኢየሱስ በመካከላችን የምንለምነው ይደርግልናል፡፡  
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #በክርስቶስ #መሰብሰብ #ጉባኤ #በኢየሱስስም #ተልእኮ #አላማ #የእግዚአብሄርመንግስት ##መንፈስ #መካከል  #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ማየት #የእግዚአብሄርመንግስት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አዲስፍጥረት #ክርስቶስ #ውክልና #እንደራሴ #አምባሳደር #ፀሎት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment