Popular Posts

Wednesday, December 27, 2017

በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ

በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ። 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡23
ይህን ሁሉ የማደርገው፣ ከወንጌል በረከት እካፈል ዘንድ፣ ስለ ወንጌል ብዬ ነው።(አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡23
በአለም ላይ ሰዎች ከትልቅ ድርጅት ስለገዙት አክሲዮን ይናገራሉ፡፡ ሰዎች በአለም ላይ ስለገዙትና ስላላቸው ቦንድ በኩራት ይናገራሉ፡፡ ይህ ሁሉ ለምድር ይጠቅማል፡፡
ሰው ግን የታወቁ የምድር ማህበሮች ማህበርተኛ ሆኖ ነገር ግን በወንጌል ማህበርተኛ ካልሆነ ምስኪን ሰው ነው፡፡
የምድር ጉዟቸውን መልስ ብለው ሲያዩ ፎቅ አልሰራሁም ታዋቂ አልሆንኩም ውድ መኪና አልነዳሁም ነገር ግን በህይወቴ ዘመን ሁሉ ቤተክርስትያንን ደግፌያለሁ የሚሉ የተባረኩ ሰዎች አሉ፡፡
የምድር ጉዟቸውን መለስ ብለው ሲያዩ ተምሬ ዶክተር አልሆንኩም ነገር ግን ወንጌልን ለመስበክ ህይወቴን ሙሉ ሰጥቼያለሁ በማለት በህይወታቸው የሚረኩ ሰዎች አሉ፡፡
እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ። ሉቃስ 16:9
አላገባሁም አልወለድኩም ነገር ግን በህይወቴ ሁሉ የእግዚአብሄርን ቤተክርስትያን የወንጌል ስራ ስደግፍ ኖሬያለሁ የሚሉ በሚገባ የተኖረ ህይወት የሚኖራቸው ሰዎች አሉ፡፡
በምድር ላይ የምንም ማህበር አባል ያልሆኑ የወንጌል ግን ማህበርተኛ ለመሆን ህይወታቸውን የሚያፈሱ ጉልበታቸውን ገንዘባቸውን እውቀታቸውን ጊዜያቸውን ለወንጌል ስራ የሚሰጡ የተባረኩ ሰዎች አሉ፡፡
አሁንም በ2018 ዓም ያዳነንን ወንጌል ማህበርተኛ ለመሆን የማይጠፋ የዘላለም ሽልማት ስለሚያስገኘው ስለወንጌል ሁሉንም ለማድረግ እንወስን ፡፡
በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ። 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡23
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ወንጌል #ማኅበረተኛ #ስብከት #ቃል #ዝራ #የምድርጨው #የአለምብርሃን #የአመፃገንዘብ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment