Popular Posts

Thursday, December 28, 2017

ከዚህ ዘመን ይልቅ ያለፈው ዘመን ለምን ተሻለ?

በምድር ስንኖር ኑሮን አንድናቆምና እጅ እንድንሰጥ ሊያስፈሩን የሚመጡ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ አንዳንድ ሰው ወጥቶ ህይወትን መጋፈጥ ሲፈራ ተኝቶ መዋል ያምረዋል፡፡ ሌላው ደግሞ ቶሎ ኢየሱስ እንደገና ተመልሶ ወይም እርሱ ወደ ሰማይ ሄዶ ችግርና መከራን ማምለጥ ይመኛል፡፡ ሰው በጌታ በኢየሱስ ያመነ ሰው ወደ ሰማይ የሚሄድበት ጊዜ አለው፡፡ ላሁን ግን የሚሰራ ስራ ስላለ በዚሁ ይቀመጣል፡፡
አንዳንዴ የሰዎችን ክፋት ስናይ ዘመኑ ያስፈራናል፡፡ እግዚአብሄር ግን የሚፈልገው በዚህ በእንግድነት አገር ታምነን እንድኖር ነው፡፡
በሰማይ የሚሸነፍ የምትቋቋመውቅ ጠላት ስለሌለ ማሸነፍ የሚባለውም ገድል የለም፡፡ ጌታ የሚፈልገው እዚሁ ጠላት ያለበት ኖረህ እንድታሸነፍ ነው፡፡ እዚሁ ጭለማ አህዛብን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን በሚሸፍንበት ምድር ነው ብርሃንህን ሊያወጣ የሚፈልገው፡፡ (ኢሳያስ 60፡1-2) እዚሁ በሞት ጥላ መካከል ነው አብሮህ መሆን የሚፈልገው፡፡ (መዝሙር 23፡4) እዚሁ በጠላቶችህ ፊት ለፊት ነው ራስህን በዘይት መቀባት የሚፈልገው፡፡ (መዝሙር 23፡3) እዚሁ ደረቁ ምድር ላይ መቶ እጥፍ እንድታፈራ የሚፈልገው፡፡ (ዘፍጥረት 26፡22) በምንም ነገር እጅ እንድትሰጥ ሳይሆን በጠበበው ደጅ ታግለህ እንድትገባ ነው የሚገፈልገው፡፡ (ማቴዎስ 7፡13) በትንሽ በትልቁ የሚያለቅስ ልፍስፍስ ሳይሆን ተናጣቂ ግፈኛ እንድትሆን ነው የሚፈልገው፡፡ (ማቴዎስ 11፡12)
ለዚህ ነው በምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ ነው የሚለው፡፡
በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። መዝሙር 37፡3
ስለዚህ ነው የበፊቱን ያለፈውን ኑሮ አያሰብክ የወደፊቱ አይመርህ የሚለው፡፡ ምክኒያቱም እግዚአብሄር የሰጠህ ፀጋ ለዘመኑ ክፋት የሚበቃ ነው፡፡
እንደ ድሮ መንገድ ባይሆንም አሁንም ለጌታ የተሰጡ ሰዎች አሉ፡፡ እንደለመድከው ባይሆንም አሁንም ለጌታ መስዋእት የሚሆኑ ሰዎች አሉ፡፡ እንዳሰብከው ባይሆንም አሁንም ለጌታና ለጌታ ክብር ብቻ የሚኖሩ ሰዎች አሉ፡፡ እንደለመድነው ባይሆንም አሁንም ጌታን በሙሉ ልባቸው እያገለገሉ ያሉ ሰዎች አሉ፡፡  
እግዚአብሄር በዘመናት መካከል አይለወጥም፡፡ ዘመን ሊለወጥ ዘመን ሊከፋ ይችላል ነገር ግን የማይለወጠው እግዚአብሄር ዘመኑን ለእኛ መልካምነት ይሰራዋል፡፡
ባለፈው ዘመን መልካም ያደረገው እግዚአብሄር እንደሞተ ሁሉ ያለፈው ዘመን ለምን የተሻለ አትበል፡፡
ከዚህ ዘመን ይልቅ ያለፈው ዘመን ለምን ተሻለ? ብለህ አትናገር፤ የዚህን ነገር በጥበብ አትጠይቅምና። መክብብ 7፡9-10
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ  #ስብከት #መዳን #ዘመን #እምነት #ወንጌል #ማኅበረተኛ #ስብከት #ቃል #ዝራ #የምድርጨው #የአለምብርሃን #ተነሺ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment