Popular Posts

Friday, December 22, 2017

#ኢየሱስ

የገና በአል ትርጉም የተረሳ ይመስላል፡፡ የገና በአል ሲታሰብ መብላት ከታሰበ ፣ የገና በአል ሲታሰብን መጠጣት ከታሰበ ፣ የገና በአል ሲታሰንብ መልበስ ከታሰበ ፣ የገና በአል ሲታሰብ የገና ዛፍ ከታሰበ የገና በአል ሲታሰብ ከረሜላ እና ቸኮሌት ከታሰበ ፣ የገና በአለ ሲታሰብ ጣፋጭ ብስኩትና ኬክ ከታሰበ ፣ የገና በአል ሲታሰብ እረፍትና መዝናናት ከታሰበ ፣ የገና በአልዕ ሲታሰብ ዘፈንና ዳንራ ከታሰበበ ፣ የገና በአል ሲታሰብ መጠጣትና መስከር ከታሰበ ምንም ሃይማኖተኛ ብንሆን የገናን ትርጉም አናውቀውም ማለት ነው፡፡
ገና የሚበላበት የሚጠጣበት የሚዘፈንበት የሚጨፈርበት አይደለም፡፡ ገና እግዚአብሄር ለሰዎች የሰጠው ስጦታ ኢየሱስ የሚዘከርበት እግዚአብሄር የሚመሰገንበትና በስጦታው ምክኒያት ያገኘነው የክርስትና ነፃነት በአል የሚደረግበት ጊዜ ነው፡፡ ገና የእግዚአብሄርን ስጦታ የማክበርበት ጊዜ ነው፡፡ ገና የእግዚአብሄርን ስጦታ የምናጣጥምበት ጊዜ ነው፡፡  
የገና ምክኒያት ኢየሱስ ነው፡፡
ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ። ማቴዎስ 1፡21
የገና ምክኒያት እግዚአብሄር ለሰው ልጆች ስጦታ መስጠቱ ነው፡፡
በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ዮሃንስ 3፡16
የገና ምክኒያት ስጦታውን የተቀበሉ ከሃጢያት መዳናቸው ነው፡፡
እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤ ቲቶ 3፡5
የገና በአል በእግዚአብሄር ስጦታ ከእግዚአብሔር ጋር መታረቃችን ነው፡፡
እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡19
የገና በአል ኢየሱስን የተቀበልን የእግዚአብሄር ልጅ መሆናችን ነው፡፡
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡12
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ገና #በዓል #ፍቅር #ተስፋ #ደስታ #መስዋእት #ሃጢያት #መዳን #ነፃነት ## #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  #ኢየሱስ #ጌታ

No comments:

Post a Comment