Popular Posts

Saturday, December 30, 2017

ለነገ (ለሚመጣው አመት) አትጨነቁ

ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል። ማቴዎስ 6፡34
በጌታ ለመኖርና ኢየሱስን ለመከተል እያንዳንዱ ቀን ተግዳሮት አለው፡፡ እያንዳንዱ ቀን የሚመጣው ከተወሰነ ተግዳሮት ጋር ነው፡፡ ይብዛም ይነስም ተግዳሮት ይዞ የማይመጣ ቀን የለም፡፡ ሁሉም ቀን የሚመጣው የራሱ የተግዳሮት ድርሻን ይዞ ነው፡፡
ቀን ይዞ ለሚመጣው ተግዳሮት የሚመጥን ፀጋ በቀን ውስጥ ይለቀቃል፡፡ ለእያንዳንዱ ቀን ተግዳሮት የሚበቃ የእግዚአብሄር ፀጋ በእያንዳንዱ ቀን ውስጥ አለ፡፡ እያንዳንዱ ቀን የራሱ ድርሻ ተግዳሮትና ለዚያ ተግዳሮት የሚበቃ የራሱ ድርሻ የሚያስችል ሃይል አለው፡፡
በነገ ውስጥ የሚለቀቀውን ፀጋ ዛሬ ማየትና መለማመድ አንችልም፡፡ ወይም ዛሬ ላይ ቆመን ነገር መኖር ወይም ማስተካካል ወይም ደህና ማድረግ አንችልም፡፡ በዛሬ የሚለቀቀው የሚያስችል የእግዚአብሄር ሃይልን የምንለማመደው በዛሬ ውስጥ ያለውን ተግዳሮት ለማለፍ ብቻ ነው፡፡
ሰው የነገን ተግዳሮት በዛሬ ፀጋ ሊጋፈጠው በመሞከር ይጨነቃል፡፡ የዛሬን ተግዳሮት ብቻ ለመኖር ከነገ ተግዳሮት ጋር ላለመቀላቀል  መረጋጋት ይጠይቃል፡፡ የዛሬን ተግዳሮት በዛሬ ፀጋ ተወጣውና ለጥ በል፡፡ ስለነገ አትጨነቅ፡፡ ስለነገ ባልተለቀቀ ፀጋ ውስጥ ሆነህ ስነገ መጨነቅ ከንቱ ነው፡፡  ስለነገ ለማሰብ ትክክለኛው ጊዜ ነገ ነው፡፡ ነገ ላይ ተግዳሮቱም ይታወቃል ፀጋውም ይገለጣል፡፡ ነገ ላይ ስለነገ ማሰብ ውጤታማ እቅድ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ስለነገ መጨነቅ ብክነት ነው፡፡
ነገ የሚመጣው በሬሱ ጊዜ ነው፡፡ ነገ የሚመጣው ከራሱ ተግዳሮትና ከራሱ ፀጋ ጋር ነው፡፡ ነገ ሲመጣ ለነገ የሚሆን እምነት አብሮት ይመጣል፡፡ ነገ ሲሆን ለነገ ተግዳሮት የሚሆን ፀጋ ይለቀቃል፡፡ ለዚያም ነው ብዙ ጊዜ የተጨነቅንበት ነገር ጊዜው ሲደርስ ሸክሙ የሚበነው፡፡
እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም። ገላትያ 3፡25
ስለነገ ማድረግ የምትችለው አንድ ነገር የሚያስጨንቅህን በጌታ ላይ መጣል ብቻ ነው፡፡ ስለነገ የሚያስጨንቅህን በእርሱ በእግዚአብሄር ላይ ከመጣል ውጪ ውጤታማ ነገር የለም፡፡ አባታችን እግዚአብሄር አንደሆነ እንደ እኛ የታደለና መጨነቅ የሌለበት ሰው የለም፡፡
ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል። ማቴዎስ 6፡34
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ጭንቀት #ነገ #ማረፍ #ጣሉ #ክፋት #ፀጋ #ምናን ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment