Popular Posts

Saturday, July 29, 2017

በተግባር እግዚአብሔርን መምሰል

እግዚአብሔርን መምሰል እንደ እግዚአብሔር ማሰብ ነው
አንድ ሰው ሲናገር የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስብና የሚያሰላስል ሰው እንደእግዚአብሔር ያስባል በማለት የእግዚአብሔርን ቃል ማሰብ እግዚአብሔርን እንደምንመስል እንዴት እንደሚረዳን ተናገረ፡፡
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2
በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ። ኤፌሶን 4፡23-24
እግዚአብሔርን መምሰል እግዚአብሔር እንደሚያየው ማየት ነው
እግዚአብሔርን የምንመስለው በእይታችን ነው፡፡ አግዚአብሔር የሚያየውን ካየን እግዚአብሔርን እንደምሳለን፡፡ የእግዚአብሔር እይታ በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ ተቀምጧል፡፡ የእግዚአብሔር እይታ የእግዚአብሔር ቃል እይታ ነው፡፡ ነገሮችን እንደእግዚአብሔር ቃል ካየን እግዚአብሔር የሚየየውን በማየት እግዚአብሔርን እንመስላለን፡፡ እግዚአብሔር እንደሚያየው ካላየን እግዚአብሔርን መምሰል በፍጹም አንችልም፡፡
እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥ 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡6-7
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17
እግዚአብሔርን መምሰል እግዚአብሔር እንደሚወደው መውደድ ነው
የእግዚአብሔር ፍቅር የእንካ በእንካ ፍቅር አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር ፍቅር የሚሰጥ የሚያካፍል የሚራራ ጠላቶቹን የሚወድ ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለመምሰል በፍቅሩ እርሱን መምሰል አለብን፡፡
የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ። ማቴዎስ 5፡46-48
ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል። እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል። 1ኛ ዮሃንስ 4፡11-12
እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥ ኤፌሶን 5፡1
እግዚአብሔርን መምሰል እግዚአብሔር እንደሚናገረው መናገር ነው፡፡
ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ . . . ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን። 1ኛ ጴጥሮስ 4፡11
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #ጌታ #መከተል #መከተል #መምሰል #እግዚአብሔርንመምሰል #ቃል #ተማሪ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ነፍስንመካድ #መፅሃፍቅዱስ #ተከታይ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment