Popular Posts

Saturday, July 15, 2017

ጌታን ያዘገየው

እግዚአብሄር ኢየሱስ በመስቀል ላይ እንዲሰቀልና የሰው ልጆችን የሃጢያት እዳ ሁሉ እንዲከፍል የላከው ሰዎች እንዳይጠፉና ለዘላለም ከእግዚአብሄር እንዳይለያይ ነው፡፡
መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል። ቲቶ 2፡14
እግዚአብሄር የሰዎችን ጥፋት አይወድም፡፡ እግዚአብሄር በሰዎች ላይ ያለው አላማ ፍቅር ነው፡፡
ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው። 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፡3-4
ኢየሱስን ከመቀበላችን በፊት ኢየሱስ ተመልሶ ያለመጣው እኛ እንድድን ነው፡፡ ሁሉ ንስሃ እንዲገቡ ወዶ ይታገሳል፡፡
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል። 2ኛ ጴጥሮስ 3፡9
በአለም ላይ ያለነው ኢየሱስ በዘገየበት ጊዜ የመንግስቱን ወንጌል እንድንሰበክ ነው፡፡ ይህ ወንጌል ከተሰበከ በኋላ የአለም መጨረሻ ይሆናል፡፡  
እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤ 1ኛ ጴጥሮስ 2፡9
ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል። ማቴዎስ 24፡14
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ወንጌል #ስብከት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመናገር #ኢየሱስይመጣል #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment