Popular Posts

Thursday, July 13, 2017

የክብር ፈተና

ደግሞ ዲያብሎስ እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ ወሰደው፥ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም አሳይቶ፦ ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው። ማቴዎስ 4፡8-9
ሰይጣን ሰዎችን ከሚፈትንበት መንገድ አንዱ የክብር ፈተና ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሄር ቃል ውስጡ ከሌለ ክብር ለማግኘት ሲፈተን ይወድቃል፡፡ ለስጋችን ስልጣንና ሃይል ይጣፍጣል፡፡ ሰው ስልጣንን ለማግኘት ሃያል ሰው ለመሆን ሲመኝ በሰይጣን ወጥመድ ውስጥ ይወድቃል፡፡
ሰው ከስልጣንም ከክብርም ከሃይልም በላይ በእግዚአብሄር ቃል መኖር አለበት፡፡ በምንም መልኩ ስልጣን ላግኝ የሚል ሰው በሰይጣን ወጥመድ መውደቁ አይቀርም፡፡ በአራዳም በፋራም ብዬ ሃይል ላግኝ የሚል ሰው የጊዜ ጉዳይ እንጂ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡
ስጋዊ ባህያችን ክብር ፣ ስልጣንና ሃይልን ይጠማል፡፡ ስጋዊ ባህሪያችን በምንም በምንም የሚመጣውን ክብርን ፣ ትልቅነትን ፣ ሃይልንና ስልጣንን ይፈልጋል፡፡ ስጋዊ ባህሪያችን ሌላውን ለመብለጥ ክብርን ፣ ትልቅነትን ፣ ሃይልንና ስልጣንን ይመኛል፡፡ ስጋዊ ባህሪያችን በእግዚአብሄር ላይ ላለመታመን አማራጭ ሃይልን ይፈልጋል፡፡ ስጋ እግዚአብሄርን ከመጠበቅ ይልቅ አቋራጭ ክብርን ይጠማል፡፡ ሰይጣን ደግሞ ሰውን ለማሰገድ የሰውን ስጋዊ ምኞት ይጠቀማል፡፡ ከምንም በላይ ክብርን የሚፈልግ ሰው በተዘዋዋሪ ለሰይጣን ይሰግዳል፡፡
. . . ከአንዱም ከእግዚአብሔር ያለውን ክብር የማትፈልጉ፥ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ? ዮሃንስ 5፡44
ሰው የክብርን ፈተና የሚያልፈው በእግዚአብሄር ቃል የሚመጣውን ክብር ብቻ ሲፈልግ ነው፡፡ ሰው የክብርን ፈተና የሚያልፈው ከእግዚአብሄር ብቻ የሚገኘውን ክብር ሲፈልግ ነው፡፡ ሰው የክብርን ፈተና የሚንቀው ሰይጣን ስጋን ተጠቅሞ እንደሚመለክ ሲያውቅ ነው፡፡
ዲያብሎስም ረጅም ወደ ሆነ ተራራ አውጥቶ የዓለምን መንግሥታት ሁሉ በቅጽበት አሳየው። ዲያብሎስም፦ ይህ ሥልጣን ሁሉ ክብራቸውም ለእኔ ተሰጥቶአል ለምወደውም ለማንም እሰጠዋለሁና ለአንተ እሰጥሃለሁ፤ ስለዚህ አንተ በእኔ ፊት ብትሰግድ፥ ሁሉ ለአንተ ይሆናል አለው። ሉቃስ 4፡5-7
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #አምላክ #ፈተና #ክብር #ትግስት #ስልጣን #ሃይል #ደስታ #ምስጋና #ፅናት #ጥበብ #እምነት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment