Popular Posts

Tuesday, July 18, 2017

የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ

እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ። ሉቃስ 16:9
በእግዚአብሄር እይታ ለወንጌል ስራ ፣ ለእግዚአብሄር መንግስት ጥቅም የማይውል ማንኛውም ገንዘብ የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
በእግዚአብሄር እይታ ለእግዚአብሄር መንግስት ዋነኛ አላማ ለሆነው ሰዎችን የማዳን ስራ የማይውል ገንዘብ ሁሉ የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው። 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፡3-4
ለዘላላማዊ ህይወት አላማ የማይጠቅም ማንኛውም ሃብት የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡ ሰዎችን ለማዳን የማንጠቀምበት ለሰዎች ብርሃን ለመሆን የማንጠቀምበትና የምድር ጨው ለመሆን የማይጠቅመን ማንኛውም ሃብት የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
ለሰዎች መልካምን አድርጋላቸው በህይወታችን መስክረን የእግዚአብሄን መልካምነት አሳይተናቸው ለጌታ ለመማረክ የማይጠቅመን  ማንኛውም ገንዘብ የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
ራቁታችንን ወደምድር መጥተናል ራቁታችንንም እንመለሳለን፡፡ በምድር ላይ የምናገኘው ለእግዚአብሄር መንግስት ስራ የማይጠቅም ገንዘብ ሁሉ ከዘላለማዊ ህይወት አንፃር ከንቱ ገንዘብ ነው፡፡  
በምድር ያከማቸነው በመልካም ስራ ወደ መንግስተ ሰማያት የማንልከው ገንዘብ ጥለነው የምንሄደው ገንዘብ ሁሉ የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
እውነተኛውን ሕይወት ይይዙ ዘንድ፥ ለሚመጣው ዘመን ለራሳቸው መልካም መሠረት የሚሆንላቸውን መዝገብ እየሰበሰቡ፥ መልካምን እንዲያደርጉ በበጎም ሥራ ባለ ጠጎች እንዲሆኑ፥ ሊረዱና ሊያካፍሉም የተዘጋጁ እንዲሆኑ ምከራቸው። 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡18-19
በመልካም ስራ ያልመነዘርነው ገንዘብ በመልካም ስራ ባለጠጋ ያላደረገን ገንዘብ በብር ተከምሮ ያለ ገንዘብ የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤ ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ ማቴዎስ 6፡19-20
ልባችንን ወደ ሰማይ የማይስበን ገንዘብን ፣ ልባችንን ወደ ምድር የሚስበን ገንዘብና ልባችንን ወደ ሰማይ እንዳናተኩር የማያደርገን ገንዘብ የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። ማቴዎስ 6፡20-21
ሰዎችን ለዘላለም ህይወት የማንማርክበት ፣ ምድር ላይ ጥለነው የምንሄደው ፣ በመሬት ስበት ምክኒያት ወደሰማይ ይዘነው የማንሄደው ፣ በምድር ላይ ብቻ በዘላለማዊ ሃብት የምንመነዝረውና በምድር ላይ ብቻ ዋጋ ያለው ገንዘብ ሁሉ የአመፃ ገንዘብ ነው፡፡
እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ። ሉቃስ 16:9
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ወንጌል #ስብከት #ቃል #ዝራ #የምድርጨው #የአለምብርሃን #የአመፃገንዘብ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment