Popular Posts

Thursday, May 25, 2017

እምነት ሲገለጥ


እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው። ዕብራውያን 11፡1
የሚታይ አለምን አለ የማይታይ አለም አለ፡፡ እምነት የማይታየው አለም ውስጥ ምን እየተሰራ እንደሆነ የምናይበትና መንገድ ነው፡፡ እምነት በተፈጥሮአዊ አይናችን የማይታየው አለም ውስጥ ምን እንዳለ በመንፈሳዊ አይናችን አይተን የምናረጋግጥበት መንገድ ነው፡፡
ይህ የምንኖርበት አለም ያልነበረበት ጊዜ ነበር፡፡ ይህ የምንኖርበት አለም እንኳን የመጣው ከማይታየው አለም ነው፡፡ አለም የተፈጠረው በማይታየው በእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡   
ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን። ዕብራውያን 11፡3
ሰው ካላየ ማረጋገጥ አይችልም፡፡ የምናየውን እንዳለ እርግጠኛ እንሆናለን፡፡ እምነት የሚያስረግጥ ማረጋገጫ ነው፡፡ እምነት በተፈጥሮ አይናችን የማናየውን ነገር በመንፈሳዊ አለም እንዳለ የሚያረጋገጥልን ማረጋገጫ ነው፡፡ እምነት በተፈጥሮ አይናችን የማናየውን ነገር የምናይበት መንገድ ነው፡፡ እምነት በአምስቱ የስሜት ህዋሶቻችን የማንደርስበትን አለም የሚያይና ምን እንዳለ የሚያረጋግጥልን ነገር ነው፡፡
እምነት ከሚታየው አለም አልፎ የማይታየውን ዘላለማዊውን አለም የምናይበትና የምናረጋግጥበት ብቸኛው መንገድ ነው፡፡
የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ . . . የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 4፡17
አሁን ያለን ማንኛውም እውቀት ሁሉ የመጣው ካስረዳን ሰው ነው፡፡ እምነት የማናየውን ነገር የሚያስረዳ ነው፡፡ እምነት የሚታየው አለም ሁሉ ምንጭ በሆነው በመንፈሳዊ አለም ያለውን ነገር አይቶ የሚያስተምረን የሚያስረዳን አስረጂ ነው፡፡ እምነት የመንፈሳዊውን አለም እውቀት የሚሰጠን አስተማሪ ነው፡፡
የማይታየውን አለም የምናይበት ብቸኛው መንገድ የእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስንረዳ መንፈሳዊውን አለም እንረዳለን፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስንሰማ የማይታየውን አለም እንሰማለን፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስናይ የማይታየውን አለም እናያለን፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ተስፋ #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment