Popular Posts

Monday, May 15, 2017

በፍቅር የሚሠራ እምነት

በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ፥ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና። ገላትያ 5፡6
እምነት እንዲሰራ የሚያደርገው ፍቅር ነው፡፡ እምነት የሚያስፈልገውም የፍቅርን ህይወት እንድንኖር ነው፡፡ እምነት ከፍቅር ተለይቶ አይሰራም፡፡ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል ያለው ያው ጌታ ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገው ውደድ ብሏል፡፡
ሰው እምነት ቢኖረው እንዲሰራ የሚያደርገው ፍቅር ግን ከሌለው ከንቱ ነው፡፡ ሰው እምነት ቢኖረው የእምነቱ ሃይል ትክክለኛ ቦታ ላይ እንዲውል የሚያደርገው ፍቅር ከሌለው ከንቱ ነው፡፡ እምነትን ወደ ትክክለኛ ቦታ የሚመራው ፍቅር ነው፡፡
ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። 1 ቆሮንቶስ 12፡1-2
በእምነት ስለምናደርገው ማንኛውም ነገር መነሻ ዝንባሌው ፍቅር መሆን አለበት፡፡ በፍቅር ባህሪ ያልተገራ የእምነት ሃይል አይሰራም፡፡
 ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ፍቅር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ፍርሃት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #መውደድ #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment