Popular Posts

Sunday, May 21, 2017

የሚያገለግለኝም ቢኖር አብ ያከብረዋል

የሚያገለግለኝ ቢኖር ይከተለኝ፥ እኔም ባለሁበት አገልጋዬ ደግሞ በዚያ ይሆናል፤ የሚያገለግለኝም ቢኖር አብ ያከብረዋል። ዮሐንስ 12፡26
እግዚአብሄርን ማገልገል እጅግ የከበረ ነገር ነው፡፡
እንዲያውም የሰው የመጨረሻው የክብር ደረጃ መሰረታዊ ፍላጎትን እያሟላ ጌታን መከተልና ነው፡፡ ይህ የሚቀናበት ሰው ነው የሚባለው ሰው መሰረታዊ ፍላጎቱን አሟልቶ ጌታን የሚወድና የሚያገለግል ሰው ነው፡፡
መሰረታዊ ፍላጎቱን አሟልቶ ጌታን ከማገልገል በላይ የሆነ ምንም የክብር ደረጃ የለም፡፡ በክርስትና ሚሊየነርነትና ቢሊየርነት መሰረታዊ ፍሎጎትን አሟልቶ ጌታን ተከትሎ መኖር ነው፡፡
ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ ወደ ዓለም ምንም እንኳ አላመጣንምና፥ አንዳችንም ልንወስድ አይቻለንም፤ ምግብና ልብስ ከኖረን ግን፥ እርሱ ይበቃናል። 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡6-8
የመጨረሻ የከበረ ሰው የሚያደርገው ጌታን መከተል ነው፡፡ በክርስትና የስኬት ጣራ ጌታን ማገልገል ነው፡፡ በክርስትና አብ የሚያከብረው ሰው መሰረታዊ ፍላጎቱን በማሟላት ለጌታ የሚኖር ሰው ነው፡፡ በክርስትና እጅግ የተሳካለት ሰው መሰረታዊ ፍላጎቱን አሟልቶ እግዚአብሄርን መስሎ የሚኖር ሰው ነው፡፡
መሰረታዊ ፍላጎቱን አሟልቶ ጌታን የሚከተለው ሰው በክብር ከማንኛውም ባለጠጋ ፣ ዝነኛና ሃያል ሰው ይበልጣል፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ጌታንመከተል #ጌታንማገልገል #ጌታንመውደድ #ስኬት #ክንውን #እግዚአብሄርንመምሰል #ቃል #ማሰላሰል #አእምሮ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ብፅእና  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment