Popular Posts

Thursday, May 4, 2017

የእግዚአብሄር ፀጋ እንዲሰራልን የሚያደርጉ ቁልፎች

የእግዚአብሄር ፀጋ በሰው ህይወት የሚገለፅ የእግዚአብሄር ችሎታ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ፀጋ በሰው የማንችለውን የሚያስችል የእግዚአብሄር ሃይል ነው፡፡ የእግዚአብሄር ፀጋ በሰው ህይወት ውስጥ የሚሰራ የእግዚአብሄር ብቃት ነው፡፡ እግዚአብሄር ለጠራን ለማንኛውም ነገር ብቁ የሚያደርገን የእግዚአብሄር ችሎታ ፀጋ ነው፡፡
ሐዋሪያው ጳውሎስ ያንን ሁሉ የእግዚአብሄር ስራ የሰራው በእግዚአብሄር ፀጋ እንደሆነ ይናገራል፡፡ እንዲያውም ከሁሉ በላይ ደከምኩ ይልና የደከምኩት እኔ አይደለሁም የእግዚአብሄር ፀጋ ነው እንጂ ይላል፡፡
ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም። 1ኛ ቆሮንቶስ 15፡10
በህይወታችን የእግዚአብሄርን ስራ ለመስራት የምንችለው በራስ ችሎታ ሳይሆን በእግዚአብሄር ፀጋ ነው፡፡
በእውነት እግዚአብሄር በህይታችን የሚፈልገውን ነገር ለማድረግ የእግዚአብሄር ፀጋ ይጠይቃል፡፡ ካለ እግዚአብሄር ፀጋ የሚደረግ ምንም የእግዚአብሄር ስራ የለም፡፡ እንዲሁም በእግዚአብሄር ፀጋ ደግሞ የማይቻል ምንም አስቸጋሪ ነገር የለም፡፡
በእኛ ፋንታ ይህ ፀጋ እንዲሰራልን ማድረግ የምንችልባቸው መንገዶች  
1.      ትህትና

የእግዚአብሄር ፀጋ በእኛ ፋንታ እንዲደክም ለማድረግ ትህትና ይጠይቃል፡፡ ፀጋን የተሞላ ትእቢተኛ ሰው የለም፡፡ ፀጋ የጎደለው ትሁት ሰው ደግሞ አይገኝም፡፡ ከእግዚአብሄር እና ከሰው ጋር በትህትና የሚኖር ሰው የእግዚአብሄር ችሎታ በእርሱ ፋንታ እንዲሰራ እያደረገ ነው፡፡ ትሁት ሰው በእርሱ ሃይል ፋንታ የእግዚአብሄር ፀጋ ተራራውን እንዲነቅለው ለጌታ ችሎታ ስፍራን እየሰጠ ነው፡፡ ትሁት ሰው በእርሱ ምትክ እግዚአብሄር እንዲሰራ ፋንታን እየሰጠውና መንገድን እየለቀቀለት ነው፡፡    

እንዲሁም፥ ጐበዞች ሆይ፥ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ፥ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል። 1ኛ ጴጥሮስ 5፡5

2.     እምነት

የእግዚአብሄር ፀጋ በህዬታችን የሚፈሰው በእምነት ነው፡፡ የእግዚአብሄርን አሰራር ከተረዳንና ለአግዚአብሄር የሚሳነው ነገር እንደሌለ ካወቅን እግዚአብሄር የተናገረንን ነገር እናደርገዋለን፡፡ እግዚአብሄር እንድናደርግ የሚናገረን ነገር በሰው ችሎታ የሚቻል ስላልሆነ የእግዚአብሄር ችሎታ በህይወታችን አንዲሰራ እምነት ይጠይቃል፡፡ እግዚአብሄር በቃሉ የተናገረውን በተቀበልን መጠን የእግዚአብሄር የሚያስችል ብቃት በስራችን ሁሉ ያልፋል፡፡ ለመዳን የእግዚአበሄርን ቃል እንዳመንን ሁሉ በህይወት አሸናፊ ለመሆን የእግዚአብሄርን ቃል በማመን የእግዚአብሄርን ችሎታ በእኛ ፋንታ እንዲሰራ መልቀቅ ይኖርብናል፡፡  

ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ኤፌሶን ሰዎች 2፡8

3.     ራስን ማማጠን

የእግዚአብሄርን ፀጋ ተቀብለን እንዳልተቀበልን በሽንፈት መኖር እንችላለን፡፡ ይህ የሚሆነው ድካማችንን የሚሞላ የእግዚአብሄር ፀጋ በህይወታችን እያለ ነገር ግን እንደሚጎድለን እንደ ደካማ ስንኖር ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ፀጋ በከንቱ መቀበል ማለት የእግዚአብሄርን ፀጋ ተቀብለን ግን እንዳልተቀበለ በስንፍና በመኖር ሃይሉን ማባከን ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ፀጋ በከንቱ መቀበል ማለት አልችልም ብሎ እግዚአብሄር በህይወታችን የሰጠንን ሃላፊነት አለመወጣት ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ፀጋ በከንቱ መቀበል ማለት አብሮን የሚሰራ የእግዚአብሄር ፀጋ አብሮን እያለ ብቻችንን እንደምንሰራ እንደ ደካማና እንደተሸናፊ ሰዎች ራስን ማየት ማለት ነው፡፡  

አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤ አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም። ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤ 2 ቆሮንቶስ 6፡1፣3-4

4.     እውቀት

ኢየሱስን ባወቅነው መጠን ምንም ያልተሰጠን ነገር እንደሌለ እንረዳለን፡፡ ኢየሱስን ባወቅነው መጠን በመስቀል ላይ ያልተሰራ ስራ እንደሌለ እናስተውላለን፡፡ የእግዚአብሄር እውቀት የእግዚአብሄር ፀጋ በእኛ ፋንታ እንዲሰራ እድልን እንድንሰጠው ያደርገናል፡፡ የእግዚአብሄር እውቀት በራሳችን ጉልበት እንዳንታገልና ለእግዚአብሄር ፀጋ እድሉን እንድንሰጥ ያስተምረናል፡፡

የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2 ጴጥሮስ 1፡2-3

5.     ፀሎት

የእግዚአብሄርን ፀጋ ለእኛ እንዲሰራልን የምናደርግበት መንገድ ፀጸሎት ነው፡፡ ስንፀልይ እግዚአብሄ ምሪትን ይሰጠናል፡፡ ስንፀልይ እግዚአብሄር እየሰራ ያለውን ያሳየናል፡፡ ስንፀልይ እግዚአብሄር የሚሰራውን በመረዳት ከእግዚአብሄር ጋር አብረን እንሰራለን፡፡ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብናልፍ ልባችንን ለእርዳታ ወደ እግዚአብሄር ካነሳን የእግዚአብሄር ሃይል በእኛ ፋንታ ይሰራል፡፡

እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #እውቀት #ምስጋና #ትህትና #ልብ #እምነት #ፀሎት #ማማጠን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment