Popular Posts

Monday, May 29, 2017

የፀጋ ቃል

ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ። ኤፌሶን 4፡29
ፀጋ የሚያስችል ነፃ ስጦታ ነው፡፡ ፀጋ የሚያስችል ሃይል ነው፡፡ ፀጋ የሚያበቃ ችሎታ ነው፡፡ ፀጋ የሚያስችል ሃይል ነው፡፡ እንደ ክርስቲያን የፀጋ ቃል ብቻ ከአፋችንም እንዲወጣ ታዘናል፡፡
እግዚአብሄር በመንፈሱ በተለያየ ፀጋ አሳድጎናል፡፡ እግዚአብሄር በፀጋው ለውጦናል፡፡ እግዚአብሄር በፀጋው ካለንበት አውጥቶናል፡፡ በፀጋው ከብዙ ነገር አሻግሮናል፡፡  
እግዚአብሄር በቃላችን ውስጥ ታላቅ ሃይልን አስቀምጧል፡፡ እኛ ውስጥ የተጠራቀመው ፀጋ በቃላችን በኩል ሌሎችን በህይወታቸው ካለው ነገር እንዲያወጣቸው ያስፈልጋል፡፡ በቃላችን ውስጥ ያለው ፀጋ መንፈሳዊ ጉልበትን የሚሰጥ ምግብ ነው፡፡ የሚሰሙን በቃላችን በኩል የእግዚአብሄርን ፀጋ ይመገባሉ፡፡ እኛን ያበረታን ፀጋ በቃላችን በኩል ለሌሎች ይተላለፋል፡፡ የሆነውን የሆንበትን ፀጋን ለሌሎች ማካፈል እንችላለን፡፡      
ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ። ኤፌሶን 4፡29
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #ንግግር #ቃል #አንደበት #እውቀት #ምስጋና #ትህትና #ልብ #እምነት #ፀሎት #ማማጠን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ


No comments:

Post a Comment