Popular Posts

Thursday, July 20, 2023

አንድ የሚያደርገን



ከሚለያየን ነገር ይበልጥ አንድ የሚያደርገን ነገር ይበዛል፡፡ አንድ የሚያደርገን ላይ ካተኮርን አንድ የማንሆንበት ምንም ምክኒያት የለም፡፡

አንድ የሚያደርገን በእያንዳንዳችን ላይ ያለው የእግዚአብሔር አላማ ነው፡፡ አንድ የሚያደርገን የተሰጠን ተመሳሳይ ተልእኮ ነው፡፡ አንድ የሚያደርገን ለአንድ መንግስት መስራታችን ነው፡፡ አንድ የሚያደርገን አንድ ጦርነት መዋጋታችን ነው፡፡ አንድ የሚያደርገን የግብ አንድነታችን ነው፡፡

የእግዚአብሔር ነገር አንድ ካላደረገን ምንም ነገር አንድ ሊያደርገን አይችልም፡፡ የእግዚአብሔር ነገር አንድ ካደረገን ደግሞ አንድ ላንሆን አንችልም፡፡

በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደ ተጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፤ አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤ ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡3-6

#ኢየሱስ #ጌታ #አንድ #ፍቅር #አንድነት #ህብረት #አካል #ቤተክርስቲያን #መፅሐፍቅዱስ #ቃል #እግዚአብሔር #መተባበር

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

 

No comments:

Post a Comment