Popular Posts

Saturday, July 29, 2023

አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ! ክፍል 1

 


“አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ፥ እርሱም ግብዝነት ነው።” የሉቃስ ወንጌል 12፡1

ኢየሱስ በምድር በተመላለሰበት ጊዜ “አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ” በማለት ደቀመዛሙርቱን በብርቱ ያስጠነቅቃቸው ነበር፡፡ ኢየሱስ በአፅንኦት ከፈሪሳዊያን እርሾ ተጠበቁ ብሎ ያስጠነቀቀበት ምክኒያቱ የፈሪሳዊያን ትምህርት ደቀመዛሙርቱን በክርስቶስ እውነተኛ እውቀት ፍሬ ቢስ ሊያደርገን የሚችል አደገኛ አካሄድ ስለሆነ ነው፡፡

የፈሪሳዊያን ትምህርት ማለት በውጫዊ ነገር ላይ ብቻ ያተኮረ የአስመሳይነት ትምህርት ነው፡፡ የፈሪሳዊያን ትምህርት ማለት በህይወት መውጫ በሆነው በዋናው በልብ ሁኔታ ላይ ያላተኮረ ነገር ግን በውጫዊ አነጋገር እና አለባበስ ላይ ብቻ ያተኮረ የእውነተኛው መንፈሳ ህይወት ርካሽ ማስመሰያ ትምህርት ነው፡፡

የፈሪሳዊያን ትምህርት ለታይታ ብቻ የሆነ በእውነተኛው መንፈሳዊ ህይወት ላይ የማያተኮር ትምህርት ነው፡፡ የፈሪሳዊያን ትምህርት ልብን የማይፈትሽ ለሃይማኖት መልክ እንጂ ለመንፈሳዊነት ምንም ግድ የሌለው ትምህርት ነው፡፡

የፈሪሳዊያን ትምህርት የሃይማኖት መልክ ያለው የእግዚአብሔርን ሃይል የካደ ትምህርት ነው፡፡

የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ። 2 ወደ ጢሞቴዎስ 3፡5

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

#ኢየሱስ #ጌታ #ፈሪሳዊ #ግብዝነት #የአምልኮትመልክ # #ፃፎች #ቤተክርስቲያን #መፅሐፍቅዱስ #ቃል #እግዚአብሔር #ሰዱቃዊያን


No comments:

Post a Comment