Popular Posts

Sunday, January 28, 2018

ራስን መግዛት በሰይጣን ላይ በርን ይዘጋል

ሰይጣን የህይወት ጠላት ነው፡፡ ሰይጣን ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው እንጂ ስለሌላ አይመጣም፡፡ ሰይጣነ ስራው መስረቅ ማረድና ማጥፋት ነው፡፡ ሰይጣን ከዚህ ውጭ ስራ የለውም፡፡ ሰይጣን ተልእኮዬን ከግብ አደረስኩ የሚለው ሰዎች ሲሰረቁ ፣ ሲታረዱና ሲጠፉ ነው፡፡
ሰይጣን ደግሞ ይመጣል፡፡ ሰይጣን ይሰራል፡፡  
የመንግሥትን ቃል ሰምቶ በማያስተውል ሁሉ፥ ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው። ሉቃስ 8:12
ኢየሱስ የዚህ አለም ገዢ ይመጣል ከእኔ አንዳች የለውም ብሎዋል፡፡
ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም፥ የዚህ ዓለም ገዥ ይመጣልና፤ በእኔ ላይም አንዳች የለውም፤ ዮሃንስ 14፡30
ኢየሱስ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ የተራበ የዚህ አለም ገዢ እየመጣ ከእኔ አንዳች የለውም ሊል እንዴት ቻለ?  
እኛስ የዚህ አለም ገዢ እየመጣ በእኛ ላይ አንዳች እንዳይኖረው ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው?
ሰይጣን በመስቀል ላይ በኢየሱስ ድል ስለተነሳ ተሸንፎዋል፡፡ ሰይጣን በግድ አስገድዶ የሚያደርገው ነገር የለም፡፡
አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው። ቆላስይስ 2፡15
ነገር ግን ሰይጣን ሰውን የሚሰርቀው የሚያርደውና የሚያጠፋው በሰው ባህሪ ድክመት ተጠቅሞ ነው፡፡ ሰውጣን ሰውን ከመስረቅ ከማረድና ከማጥፋቱ በፊት ደካማ ባህሪውን ይፈልጋል፡፡ ሰይጣን በሰው ውስጥ እንደ እግዚአብሄር ቃል ያልሆነ ባህሪ ካላገኘ ሰውን ሊሰርቅ ሊያርድና ሊያጠፋ አይቻለውም፡፡ ሰውን ለመስረቅ ሰይጣን በመጀመሪያ በሰው ውስጥ ጥላቻን ይፈልጋል፡፡ ሰውን ለማረድ ሰይጣን ቁጣን በሰው ውስጥ ይፈልጋል፡፡ ሰይጣን ሰውን ለማጥፋት መጀመሪያ ትእቢትን በሰው ውስጥ ይፈልጋል፡፡ ሰይጣን እነዚህን ባሪያት በውስጣችን ካላገኘ ይመጣል ግን ምንም ማድረግ አይችልም፡፡ ሰይጣን እነዚህን እንደ እግዚአብሄር ቃል ያልሆኑ ባህሪያት ካገኘ ህይወታችን ለመስረቅ ለማረድና ለማጥፋት ይመቸዋል፡፡
በፍቅር በሚኖር ሰው ለመጠቀም ሰይጣን አይችልም፡፡ በምህረት የሚኖረውን ሰው ለማረድ ሰይጣን አይችልም፡፡ ትሁት የሆነን ሰው ህይወት ለማጥፋት ሰይጣን አይችልም፡፡
ስለዚህ ሰይጣንን በተዘዋዋሪ መንገድ ከህይወታችን ለመከላከልና ለሰይጣን በህይወታችን ውስጥ ስፍራ ለማሳጣት ባህሪያችንን መከታታል ይኖርብናል፡፡ በህይወታችን በሰይጣን ጥቃት ላይ በር ለመግዛት በእግዚአብሄር ቃል እግዚአብሄር መምሰል መልካም ባህሪያችንን መገንባት ይኖርብናል፡፡  
ሰይጣን የሚወደውና የሚጠቀምበትን ባህሪ ከህይወታችን ካስወገድን የዚህ አለም ገዢ ይመጣል ከእኔ ግን አንዳች የለውም ማለት እንችላል፡፡
ተቆጡ ኃጢአትንም አታድርጉ፤ በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፥ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ኤፌሶን 4፡26-27
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #ደስታ #ዘር #ባህሪ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሄርህይወት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #በጎነት #የዋሃት #ራስንመግዛት #ትግስት #ትህትና 

No comments:

Post a Comment