Popular Posts

Monday, January 29, 2018

አሮጌውን ሰው አስወግዱ

ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ ኤፌሶን 4፡22
አሮጌው ሰው ስጋዊ ባህሪ ነው፡፡ አሮጌው ሰው እግዚአብሄርን የማይፈልግ የምድራዊ ሰው ባህሪ ነው፡፡ አሮጌው ሰው ለእግዚአብሄር ነገር ግድ የሌላው የተፈጥሯዊ ሰው ባህሪ ነው፡፡ አሮጌው ሰው ለመንፈሳዊ ነገር ዋጋ የማይሰጥ ሰው ባህሪ ነው፡፡ አሮጌው ሰው ከእግዚአብሄር ጋር የተጣላ ሰው ሃሳብ ነው፡፡ አሮጌው ሰው ለእግዚአብሄር የማይገዛ ሰው ሃሳብ ነው፡፡ አሮጌው ሰው እግዚአብሄርን ሊያስደስት የማይችል ሰው አካሄድ ነው፡፡
አሮጌው ሰው የስጋ ሃሳብ ነው፡፡ አሮጌው ሰው የሃጢያት ሃሳብ ነው፡፡ አሮጌው ሰው የክፉ ምኞት ሃሳብ ነው፡፡
ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው። ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤ በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም። ሮሜ 8፡6-8
አሮጌው ሰው የሚፈልገው መዝናናት ፣ መብላት ፣ መጠጣት ፣ መስከር መደሰት ብቻ ነው፡፡ አሮጌው ሰው ስለምንም ነገር ሃላፊነት መውሰድ አይፈልግም፡፡ አሮጌው ሰው በማንም እንደማይጠየቅ እንደማይፈረድበት ሃላፊነት የጎደለው ሰው አካሄድ ነው፡፡ አሮጌው ሰው ስለ ሰማይ ግድ የለውም አሮጌው ሰው አርቆ ሊያይ አይችልም አሮጌው ሰው የአሁን ሰው ብቻ ነው፡፡ አሮጌው ሰው አላማና ግን የለውንም ህይወት እንደነዳው የሚሄድ ራሱን የማይገዛ ሰው አካሄድ ነው፡፡  
መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው። ፊልጵስዩስ 3፡19
አሮጌው ሰው "ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ" እንደሚሉት አይነት ሰው ነው፡፡ ስጋ የእግዚአብሄር አላማ ፣ የእግዚአብሄር ፍቃድ ፣ ለእግዚአብሄር መኖር ፣ ጌታን መከተል ፣ ራስን መካድ ፣ ጌታን ማስደሰት የሚሉት ነገሮች አይገቡትም አይረዳቸውም፡፡
ለአሮጌው ሰው የእግዚአብሄር መንግስት የማይታይ የማይጨበጥ ነገር ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው የእግዚአብሄር ነገር ሞኝነትይ ነው፡፡
ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም። 1ኛ ቆሮንቶስ 2፡14
ለአሮጌው ሰው ፍቅር ሞኝነት ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው ራስ ወዳድነት የህይወት መንገድ ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው ስግብግብነት ህይወት ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው ትህትና ደካማነት ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው ምህረት ማድረግ አለማወቅ ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው ጥላቻ የህይወት ዘይቤ ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው መስጠት ማካፈል ማባከን ነው፡፡ ለአሮጌው ሰው ትእቢት ሃያልነት ነው፡፡   
አሮጌውን ሰው አስወግዱ ሲል በአሮጌው ሰው አካሄድ አትሂዱ ማለት ነው፡፡ አሮጌውን ሰው አስወግዱ ሲል በአሮጌው ሰው አስተሳሰብ አትመሩ እያለን ነው፡፡ አሮገውን ሰው አስወግዱ ሲል አሮጌው ሰው ዋጋ ለሚሰጠው ነገር ዋጋ አትስጡ እያለን ነው፡፡
ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ። ሮሜ 13፡14
ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ ኤፌሶን 4፡22
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #ደስታ #ዘር #ባህሪ #አሮጌውሰው #ፊተኛ #አዲሱሰው #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሄርህይወት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #በጎነት #የዋሃት #ራስንመግዛት #ትግስት #ትህትና

No comments:

Post a Comment