Popular Posts

Saturday, January 13, 2018

ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን

ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው። 1 ዮሐንስ 5፡4
እግዚአብሄር የዘላለም ንጉስ ነው፡፡ እግዚአብሄር አሸናፊ ነው፡፡
አለም በመንፈሳዊ አለም በጦርነት የተሞላች ነች፡፡ በዚህ ምክኒያት ብዙ ሰዎች በአለም ተሸንፈው ቀርተዋል፡፡
አለምን የምናሸንፈው በእድል አይደለም፡፡ አለምን የምናሸንፈው በእውቀት አይደለም፡፡ አለምን የምናሸንፈው በሃይል አይደለም፡፡ አለምን የምናሸንፈው በብልጥግና አይደለም፡፡ የአለም አሸናፊነት የምድራዊ አሸናፊነት ጉዳይ አይደለም፡፡ አለም ከእግዚአብሄር ያልተወለዱትን አዋቂዎች ፣ ሃያላን እና ባለጠጎች ሁሉ አሸንፋ ከንቱ አድርጋለች፡፡
በአለም ላይ አሸናፊ ለመሆን ብቸኛው መንገድ ከእግዚአብሄር መወለድ ነው፡፡ ከእግዚአብሄር የተወለደ ሁሉ ደግሞ አለምን ያሸንፋል፡፡
ሰው በእምነት መንፈሳዊውን አለም ካላየና ከእግዚአብሄር ጋር በእምነት ካልተገናኘ አለምን መሸነፍ በፍፁም አይችልም፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር ቃል ዳግመኛ በመወለድ ብቻ የእግዚአብሄርን መንግስት ማየትና ከንጉሱም ጋር መገናኘት ይችላል፡፡
ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ዮሃንስ 3፡3
ሰው በእምነት የዘላለሙንና የማይታየውን ካላየ በስተቀር አለምን ማሸነፍ አይችልም፡፡
የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው።2ኛ ቆሮንቶስ 4፡17-18
ሰው በእግዚአብሄር ቃል ጉልበት ካልሆነ አለምን ማሸነፍ አይችልም፡፡ ሰው የእግዚአብሄርን ቃል በመስማት በእምነት አይን ካላየ አለምን ማሸነፍ አይችልም፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17
ሰው ግን የሁሉ ነገር ምንጭ የሆነውን መንፈሳዊውን አለም ማየት ከቻለ አለምን ማሸነፍ ይችላል፡፡
ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን። ዕብራውያን 11፡3
ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው። 1ኛ ዮሐንስ 5፡4
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ሃያል #ጠቢብ #ባለጠጋ #ድልነሺ #ዳግመኛመወለድ #የእግዚአብሄርልጅ #መንፈስ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #አሸናፊ #አለቅነት #ስልጣናት #ስልጣን #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment