Popular Posts

Friday, January 19, 2018

እንኳን ለጥምቀት ህይወት አደረሳችሁ

ጥምቀት በአመት አንድ ቀን የምናስታውሰው በአል አይደለም፡፡ ጥምቀት ህይወት ነው፡፡ ጥምቀት የክርስትና ህይወይ ዘይቤ ነው፡፡
ኢየሱስ የሞተውና የተነሳው ስለእኛ ሃጢያት ነው፡፡ ኢየሱስ የሞተውና የተቀበረው እኛን ወክሎ ነው፡፡ ኢየሱስ የሞተውና የተቀበረው በእኛ ፋንታ ነው፡፡  
ኢየሱስ ስለሃጢያታችን እንደሞተና እንደተቀበረ እውቅና ስንሰጥ በውሃ እንጠመቃለን፡፡ በውሃ የመጠመቃችን ትርጉሙ ኢየሱስ ስለእኛ እንደሞተ እንደተቀበረ ማሳይ ነው፡፡ በውሃ የመጠመቃችን ትርጉሙ ኢየሱስ ስለሃጢያቴ እንደሞተልኝ እኔም ለሃጢያትና ለአለም ክፉ ምኞት ሞቻለሁ ማለት ነው፡፡  
ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን? ሮሜ 6፡3
በውሃ ስንጠመቅ ከውሃ ስር እንድምንሆንና ውሃው እኛንና ሌላውን አለም እንደሚለይ ሁሉ የጥምቀት ምሳሌነቱ ከሃጢያት መገላገላችንና መለያየታችን ሃጢያት እንደማይገዛንና ከሃጢያት ሃይል ነፃ መውጣታችን ማሳያ መንገድ ነው፡፡
እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ሮሜ 6፡4
ጥምቀት ከሃጢያት ሃይል ነፃ የወጣንበት የእግዚአብሄር አሰራር እንጂ የሃጢያት በአል አይደለም፡፡ ጥምቀት ቅድስናን የተቀበልንበት የእግዚአብሄር አሰራር እንጂ ሃጢያት የሚነግስበት በአል አይደለም፡፡ ጥምቀት ከሃጢያት ሃይል ነፃ የወጣንበት አሰራር እንጂ ሃጢያት የሚስፋፋበት በአለ አይደለም፡፡ ጥምቀት እግዚአብሄር የሚፈራበትና የሚከበርበት በአል እንጂ የሰይጣን ስራ ሃጢያትና እርኩሰት የሚስፋፋበት በአል አይደለም፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ጥምቀት #ሞት #ትንሳኤ #መቀበር #አዲስህይወት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ብፅእና  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment