Popular Posts

Wednesday, January 17, 2018

እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል

ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል። እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል። 1ኛ ዮሐንስ 4፡11-12
እግዚአብሄር ፍቅር ነው፡፡ የፍቅር ህይወት እግዚአብሄርን ይስበዋል፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ለመኖርና ለመስራት ፍቅር ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር በፍቅር ይኖራል፡፡ የፍቅር ህይወት ለእግዚአብሄር ተስማሚ ቤቱ ነው፡፡ ፍቅር ለእግዚአብሄር የፈለገውን መልካምነት ዘርቶ የሚያጭድበት ተስማሚና ለም መሬት ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰዎችን ለመባረክ በፍቅር የሚኖርን ሰው ይጠቀማል፡፡ በፍቅር ያልሆነ ነገር እግዚአብሄርን ይገፋዋል፡፡ በፍቅር የሆነ ህይወት እግዚአብሄርን ይጋብዘዋል፡፡ እግዚአብሄር ካለ ደግሞ መልካመ ነግር ሁሉ ይኖራል፡፡ እግዚአብሄር ሲኖር ህይወት ይትረፈረፋል፡፡    
እንዲሁም ጥላቻ ደግሞ ለሰይጣን ለም መሬቱ ነው፡፡ ሌባው ሊሰርቅ ሊያርድና ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም፡፡ ሰውን ለመስረቅ ለማረድና ለማጥፋት ከመጠቀሙ በፊት ሰይጣን ጥላቻን በሰው ውስጥ ይልካል፡፡ ሰው የጥላቻን ሃሳብ ከተቀበለና ጥላቻ ውስጥ ከገባ ሰይጣን በቀላሉ የመስረቅ የማረድና የማጥፋት ተልእኮውን ሊያሳካ ይችላል፡፡
ሰው በልቡ ጥላቻ ከሌለበት ደግሞ ሰይጣን በምንም መልኩ በሰው ሊጠቀም አይችልም፡፡ሰው በፍቅርና በምህረት ከተመላለስ ሰይጣን በህይወታችን መቆሚያ ቦታ ያጣል፡፡  
በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፥ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ኤፌሶን 4፡27
በግቢያችን ዝንብ እንዳይገባ ከፈለግን ዝንብን የሚስበውን ቆሻሻ ማፅዳት ወሳኝ አለብን፡፡ ዝንብ መጥቶ የሚያርፍበትና የሚላው ቆሻሻ ከሌለ ይራባል ለመኖር ያቅተዋል፡፡ ስለዚህ የዝንብ ማስወገጃ ተዘዋዋሪ መንገድ ቤትን ከቆሻሻ ማፅዳት ነው፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ሰይጣን በህይወታችን እንዲቆይ የሚያደርገው የሚበላው ቆሻሻ ነገር ጥላቻን በህይወታችን ሲያገኝ ብቻ ነው፡፡ ህይወታችን ከጥላቻ ከፀዳ ግን ቢመጣም የሚበላው ነገር ስለማያገኝና ስለሚራብ መቀመጥ አይፈልግም፡፡ ከጥላቻ የፀዳ አእምሮ ለሰይጣን አመቺ ስፍራ አይደለም፡፡ ከጥላቻ ራሱን የሚጠብቅ ሰውና ከጥላቻ የራቀ ህይወት ለሰይጣን ምንም ተዘርቶ የማይበቅልበት ጭንጫ መሬት ነው፡፡
ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል። እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል። 1 ዮሐንስ 411-12
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ  #ፍቅር #መውደድ #እግዚአብሔር #ፍፁም #እርስበርስ #ተግባር #ትጋት #ስራ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #እምነት #ምህረት #ይቅርታ #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ፍርሃት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #መውደድ

No comments:

Post a Comment