Popular Posts

Sunday, October 21, 2018

በሮች ሲዘጉ መረዳት ያለብን 3 ወሳኝ ነገሮች


በህይወታችን ይከፈታሉ ብለን የጠበቅናቸው በሮች ወይም እድሎች ላይከፈቱ ይችላሉ፡፡ በሮች ላለመከፈት የተለያየ ምክኒያቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ በሮች ያለተከፈቱበትን ምክኒያት ካወቅን ስለበሮች አለመከፈት ማድርግ የሚገባንን ትክክለኛውን ነገር እናውቃለን፡፡
በሮች ካልተከፈቱ በጠበቅነው ሁኔታ አይደለም ማለት ነው
አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሄር የተናገረንን ብንሰማም ምን እንደተናገርንም ብናውቅም ነገር ግን እንዴት በህይወታችን እንደሚፈፀም በትክክል ላንረዳው እንችላለን፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ምን ሊያደርግ እንደፈለገ ብናውቅም እንዴት እንደሚፈፅምው መንገዱን ሙሉ ለሙሉ ላንረዳው እንችላለን፡፡ 
እግዚአብሄር ለበልአም ሂድ ብሎ ከተናገረው በኋላ ፊቱ የቆመው በዚህ መክኒያት ይመስለኛል፡፡
እግዚአብሔርም ወደ በለዓም በሌሊት መጥቶ፦ ሰዎቹ ይጠሩህ ዘንድ መጥተው እንደ ሆነ፥ ተነሣ ከእነርሱም ጋር ሂድ፤ ነገር ግን የምነግርህን ቃል ብቻ ታደርጋለህ አለው። ኦሪት ዘኍልቍ 22፡20
የእግዚአብሔርም መልአክ በለዓምን፦ ከሰዎቹ ጋር ሂድ፥ ነገር ግን የምናገርህን ቃል ብቻ ትናገራለህ አለው። በለዓምም ከባላቅ አለቆች ጋር ሄደ። ኦሪት ዘኍልቍ 22፡35
እግዚአብሄር ስለ አንድ ነገር ተናገረን ማለት እግዚአብሄርን ከዚያ በኋላ ስለዚያ ነገር አንፈልገውም ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ስለአንድ ነገር ተናገረን ማለት ከዚያ ጊዜው ጀምሮ ስለዝርዝር ጉዳዪ እግዚአብሄርን እንፈልዋለን ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር አንድ ስለሚሆን ነገር ተናገረን ማለት ስለአፈፃፀሙ ጥበብን እንዲሰጠን እግዚአብሄርን አብዝተን መፈለግ አለብን ማለት ነው፡፡   
በሮች ካልተከፈቱ ጊዜው አይደለም ማለት ነው
በሮች ከተዘጉ ወደፊት ይከፈታሉ አሁን ግን የመከፈቻ ጊዜያቸው አይደለም ብለን ማሰብ እንችላለን፡፡ እግዚአብሄር ከተናገረን በሮች ይከፈታሉ፡፡ እግዚአብሄር ስለአንድ ነገር ሲናገረን ሁለት ምኞቶች በልባችን ይነሳሉ፡፡ አንደኛው ምኞት የእግዚአብሄርን ፈቃድ በመፈፀማችን ያለ ትክክለኛ ምኞት ሲሆን ሁለተኛው ምኞት ደግሞ ስጋዊ ራስ ወዳድነት የተሳሳተ ምኞት ነው፡፡ ንፁህ ምኞት ሰዎችን ስለመወደድ እና ስለማገልገል ያለ ምኞት ሲሆን ሁለተኛው ምኞት በሰዎች ስለመጠቀም ራስ ወዳድነት ምኞት ነው፡፡ ይህ ንፁህ ያልሆነው የልብ ሃሳብ እሰኪጣራ ድረስ እግዚአብሄር የተናገረን ነገር በህይወታችን ሊሆን አይችልም፡፡ እግዚአብሄር የተናገረን ነገር በህይወታችን እንዲሆን ይህ መልካም ያልሆው የልብ ሃሳብ በጊዜ ውስጥ መጥራት እና መሞት ይኖርበታል፡፡   
በሮች ካልተከፈቱ አይከፈቱም ማለት ነው
ከተባበርነው እግዚአብሄር በህይወታችን የሚፈልገውን ነገር ማድረግ ይችላል፡፡ እግዚአብሄር መክፈት የማይችለው በር የለም፡፡ በሮች ካልተከፈቱ የእግዚአብሄር ፈቃድ የለበትም ብለን ማሰብ እንችላለን፡፡ በሮች ካልተከፈቱ በዚያ በር መከፈት ለህይወታችን አደጋ አለው ማለት ነው፡፡ በሮች ካልተከፈቱ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል ማለት ነው፡፡ በሮች ካልተከፈቱ የእግዚአብሄር ፈቃድ የለበትም ብለን ማሰብ እንችላለን፡፡
ባለጠጎች ደኸዩ፥ ተራቡም፥ እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም። መዝሙረ ዳዊት 34፡10
በሮች ካልተከፈቱ የእግዚአብሄር ፈቃድ የለበትም ብለን ማሰብ እንችላለን፡፡ የእግዚአብሄር ፈቃድ ሆኖ ሰዎች ዘጉብኝ ማለት እግዚአብሄርን ማሳነስ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ፈቃድ ሆኖ ሰይጣን ዘጋው ማለት እግዚአብሄር ሁሉን አይችልም እንደማለት ነው፡፡
እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡28
በማይከፈት በር ላይ ጊዜን ማጥፋት ህይወትን ማባከን ነው፡፡ እግዚአብሄር ሁልጊዜ የተሻለ ነገር እንዳለው አውቆ ለእግዚአብሄር ድምፅ ራስን መክፈት መልካም ነው፡፡ እግዚአብሄር ያልከፈተበት ምክኒያት እንዳለው ተረድቶ ለእግዚአብሄር ቀጣይ መሪነት ራስን መክፈት ያስፈልጋል፡፡  
እግዚአብሄር እረኛችን ሆኖ ከሚያስፈልገን ነገር የምናጣው ነገር የለም ብለን ማመን አለብን፡፡ እግዚአብሄር እረኛችን ሆኖ ያጣነው ነገር ሁሉ የማያስፈልገን ነገር ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ሃያል #ሁሉንቻይ #የሚዘጋ #የሚከፍት #በር ##ፍፁም #ተመላለስ #ኤልሻዳይ #እምነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment