Popular Posts

Monday, October 15, 2018

አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህስ ከዚህ አታውጣን።


እርሱም፦ አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህስ፥ ከዚህ አታውጣን። በምድርም ፊት ካለው ሕዝብ ሁሉ እኔና ሕዝብህ የተለየን እንሆን ዘንድ አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህ፥ እኔና ሕዝብህ በአንተ ዘንድ ሞገስ ማግኘታችን በምን ይታወቃል? አለው። ኦሪት ዘጸአት 33፡15-16
ሰው የተፈጠረው ከእግዚአብሄር ጋር ለመግባትና ለመውጣት ነው፡፡
ሰው ከእግዚአብሄር ጋር መውጣትና መግባት ባቆመ ጊዜ ነገሩ ሁሉ ሞተ፡፡ ሰው እግዚአብሄርን መከተል ባቆመ ጊዜ መንገድ ጠፋበት፡፡ ሰው የህይወት ምንጭ እግዚአብሄርን መከተል ባቆመ ጊዜ ህይወት ራቀው፡፡ ሰው የብርሃን አምላክን መከተል ባቆመ ጊዜ በጨለማ ተዋጠ፡፡
የእግዚአብሄርን መልካምነት ጣእሙን የቀመሱ ሰዎች በፅናት አንተ ከልወጣህ አታውጣን  ይላሉ፡፡ የእግዚአብሄርን አብሮነት ጣእሙን የቀመሱ ሰዎች የዘወትር የልብ ጩኸት አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህስ ከዚህ አታውጣን ነው። እገዚአብሄርን የሚያውቁ ሰዎች ካለእግዚአብሄር ለአንድ ሰከንድ ካለእግዚአብሄር መውጣት አይፈልጉም፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር የተለማመዱ ሰዎች ካለ እግዚአብሄር አንድ እርምጃ መራመድ አይደፍሩም፡፡
እግዚአብሄርን የተገናኙ ሰዎች ከእግዚአብሄር ጋር ካልወጡ የህይወትን ትርጉም አያገኙም፡፡ የእግዚአብሄርን ህልውና የተለማመዱ ሰዎች ከእግዚአብሄር ጋር ካልሆነ የመውጣት አስፈላጊነት ይጠፋባቸዋል፡፡ እግዚአብሄርን ያዩት ሰዎች ካለ እግዚአብሄር ከመውጣት አለመውጣትን ይመርጣሉ፡፡
ያለ እርሱ ፈቃድ የበላ ደስ ብሎትም ተድላን የቀመሰ ማን ነው? መጽሐፈ መክብብ 2፡25
የእግዚአብሄርን ክብር ያዩ ሰዎች ካለእግዚአብሄር የሚገኝ ምንም ነገር አያጓጓቸውም፡፡ የእግዚአብሄርን አብሮነት የተለማመዱ ሰዎች እግዚአብሄር የሌለበትን ቦታ አጥብቀው ይጠየፋሉ፡፡ እግዚአብሄርን የተረዱ ሰዎች እግዚአብሄር የሌለበት ቦታ ያለውን አደጋ በእጅጉ ይፈራሉ፡፡ መዝሙረኛው እንዲህ የሚለው ስለዚህ ነው፡፡
ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ። መዝሙረ ዳዊት 84፡10
እርሱም፦ አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህስ፥ ከዚህ አታውጣን።
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የእግዚአብሄርፈቃድ #ፀሎት #ልመና #እንዲሰማን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #የእግዚአብሄርቃል #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መጠየቅ #መንበርከክ #ምስጋና

No comments:

Post a Comment